Sunday 23 March 2014

ኣሳ ጉርጉዋሪ ዘንዶ ያወጣል

በያህያ ጀማል | March 23, 2014

የነፍጠኛው ገዢ መደብ ርዝራዦች በተቻላቸው ኣቅም ሁሉ ኦሮሞና ኦሮሞነትን ለመፋለም ተሰማርተዋል። የመንግስትን ስልጣን ይዞና የነፍጠኛውን የበላይነት ተክቶ ኣገር እየመራ ያለው ወያኔ ኢህኣዴግ ቢሆንም የነርሱ ዋነኛ ጠላት ግን ዛሬም ስልጣን ኣልባው ኦሮሞ ሆኖ ቀጥሏል። የወያኔ ኢህኣዴግ መንግስት ኦሮሞን ጨምሮ የብሄር ብሄረሰቦችን ማንነት ኣምኖ መቀበሉና ይህንንም (በመጠኑም ቢሆን) የሚያረጋግጥ ፌዴራላዊ ስርኣት መዘርጋቱ ያበገናቸው የቀድሞው ኣሃዳዊ ስርኣት ናፋቂዎች ኣማራ ነን ብለው ኣፋቸውን ሞልተዋ እንደ ኣማራ ብሄር ቆመው ከመከራከር ይልቅ ዛሬም በ ‘ኢትዮጵያነት’ የማስመሰያ ካባ ነጻ ህዝቦችን መልሰው መዳፋቸው ስር ማስገባት ከማለም ኣልቦዘኑም። ዛሬም የኦሮሞው፣ የትግራዩ፣ የሲዳማው፣ የቤኒሻንጉሉ፣ የሃዲያው ወዘተ ማንነት በራሳቸው ማንነት ታፍኖ፣ ቁዋንቁዋቸው በኣማርኛ ተተክቶ ኣማራ ሆይ ማረን ብለው ኣጎንብሰው ኣንዲያመልኩኣቸው ከማለም ኣልተመለሱም።
እነዚህ የነፍጠኛው ገዢ መደብ ኣተላዎች በነርሱ እኩይ የስልጣን ጥማትና በሌሎች ላይ በሚያሳዩት ንቀት ሳቢያ ኣማራውን ሁሉ ኣንድ ላይ ደምረን እንድንጸየፍ ወይም እንድናወግዝ ይፈልጋሉ። በርግጥ የተከበረው የኣማራ ህዝብ እነዚህን ከኣብራኩ የወጡና ለሌሎች ሰላምና ነጻነት ጸር የሆኑትን ልጆቹን ገስፆ የማስታገስ ሃላፊነት የወደቀው ከማንም በላይ በገዛ ትከሻው ላይ መሆኑ ኣይካድም። ኣንዳንድ መረን የለቀቁ ተማርን ባይ የኣማራ ተወላጆች ጭራሽ በነርሱ ብሶ ‘ኦሮሞ ወደ ኢትዮጵያ የገባው በ16ኛው ክፍለ ዘመን ነው’ እያሉ ኣደገኛ ድፍረት እያሳዩን ናቸው። የተከበረው የኣማራው ህዝብ እንዲህ ባለው ኣደገኛ ድፍረት ውስጥ እጁን ከማስገባት ኣንዲቆጠብና የህዝብ ለህዝብ ክብራችንን እንደጠበቅን እንድንዘልቅ እየተመኘን ከመዘዘኞቹ ባለጉዳዮች ጋር የታሪክና የፖለቲካ ሂሳባችንን ለማወራረድ እንገደዳለን።
የኣማራው ሊህቃን ስለ ምኒልክ ጭፍጨፋና ስለ ኢትዮጵያ ኢምፓየር ኣመሰራረት ኢ ፍትሃዊነት በተነሳ ቁጥር እሱን ትተው ዘለው ቂብ የሚሉት በ16ኛው ክፍለ ዘመን ታሪክ ጉዳይ ላይ ነው። ለምኒልክ ጉዳይ ምኒልካዊ ምላሽ መስጠት ተስኖኣቸው ሃራምባና ቆቦ የሆነ ነገር መዘባረቁ ይቀናቸዋል። ምኒልክ የራሱን ኢምፓየር ለመመስረት ሲዘምት ኦሮሞውንና ሌላውን ብሄር ጨፍጭፏል ኣልጨፈጨፈም ነው ጥያቄው። ምላሹም ኣዎን ጨፍጭፎ ነበር ወይም የለም እልጨፈጨፈም ነው። ከሁለቱ መልሶች የተያዘውን ይዞ በጭብጥ መከራከር ያባት ሆኖ ሳለ ሮጠው 16ኛው ክፍለ ዘመን ላይ ጉብ ማለት ኣስቂኝ የፈሪዎች ባህሪይ ነው።
ትምህተኞቹ የነፍጠኛ ልጆች የምኒልክን ጭፍጨፋ በተመለከተ ‘ኣባቶቻችን ስህተት ፈጽመዋልና ያለፈውን ስህተታቸውን ለታሪክ ትተን በኣዲስ ወዳጅነት ለወደፊቱ የጋራ ህልውናችን እንትጋ’ የሚል በቅን የተሞላ ኣቁዋም ይይዙ ይሆናል ተብለው ሲጠበቁ ይባስ ብለው ‘ጭፍጨፋው ፍትሃዊ ነበር’ እያሉ ሽንጣቸውን ገትረው መከራከርን መርጠዋል። ይህ ኣጉል ድፍረታቸው ደግሞ የሚመነጨው ‘ኦሮሞ ወደ ኢትዮጵያ የገባው ከ16ኛው ክፍለ ዘመን በሁዋላ ነውና እንዲህ ኣይነት ወቀሳ ሊያቀርብብን ሞራል የለውም’ ከሚል የድንቁርና እምነታቸው ነው። ኢትዮጵያን የያዛችሁት በቅርብ ጊዜ ውስጥ በመሆኑ እኛ የጥንት ባለርስቶች ስንጨፈጭፋችሁ መጨፍጨፍ፣ ስንገዛችሁ መገዛት፣ ስናፍናችሁ መታፈን እንጂ ሌላ ኣማራጭ የላችሁም ሊሉን ይዳዳቸዋል። ከዚህም ኣልፎ ወራሪውን ምኒልክን ሲታገሉት የወደቁ የኦሮሞ ጀግኖችን ያላንዳች ሃፍረት ‘ከሃዲዎች’ ሲሏቸውም እየሰማን ነው። የምኒልክ ጦር ዘምቶ የያዘው መሬት ጥንታዊ መሬታችን እንጂ የኦሮሞ መሬት ኣልነበረምና በዚህ ጦርነት ላይ ኦሮሞውን ጡት መቁረጥና መስለብ ፍትሃዊና ቁዱስ እርምጃ ነው እያሉ ናቸው። ይህ ነው የመከራከሪያቸው ዋነኛው ጭብጥ።
ይህን ካልን ዘንዳ ወደ ዋናው ነጥብ እንግባ። ለመሆኑ ኦሮሞ ከ16ኛው ክፍለ ዘመን በፊት ኣገሩ ሌላ ነበር? ይህንን ኣስቂኝ ጥያቄ ለመመለስ ሲባል ወደ ጥንታዊ ታሪክ መግባት የግድ ሊሆንብን ነው። ጥንታዊው ታሪክ ስንል ቢያንስ ከኣንድ ሺህ ኣመት በፊት ስለነበረው ታሪክ ማለት ነው። ጥንታዊውን ታሪክ ስናስብ ዛሬ ኦሮሞ፣ ኣማራ፣ ወዘተ እየተባሉ በብሄር ስም ስለሚጠሩ ህዝቦች ሳይሆን የነዚህ ብሄሮች ኣባት ስለነበሩት ነገዶች ነው የምናነሳው። የቀጣናችን ጥንታዊ ታሪክ ስለ ብሄሮች ሳይሆን ስለነገዶች ነው የሚያወሳው። በነገድ ነገዳችን ስንደለደል ታዲያ ኦሮሞ ዋነኛው የኩሽ ነገድ ግንድ መሆኑን እናገኛለን። የኩሽ ነገድ የጥንታዊቷ ኢትዮጵያ (የዛሬዋን የምኒልክ ኢምፓየር ማለቴ ኣይደለም) የስልጣኔ ባለቤት ነው። የኩሽ ኢትዮጵያ ግሪኮቹ Aithiops ያሉዋት የጥቁር ህዝብ ምድር ነበረች። ይቺ የኩሽ ኢትዮጵያ ናት በመፅሃፍ ቅዱስ ውስጥ ‘ኢትዮጵያ እጆቿን ወደ እግዚኣብሄር ትዘረጋለች’ ተብላ የተጠቀሰችው። ይህ ደግሞ ከግብጽ ጀምሮ እስከ ኑቢያ ድረስ እንዲሁም በኣንዳንድ መልኩ ኣክሱምን የሚያጠቃልል የጥንት ስልጣኔ ኣሻራ ነው። በዚህ የስልጣኔ ዘመን ኣማራ፣ ኦሮሞ፣ ትግራይ… የሚባል የብሄር ኣደረጃጀት ላይ ኣልተደረሰም ነበር ብለናል። ስለሆነም ኩሾቹ ኣንደኩሽነታቸው፣ ሃበሾችም (ሁዋላ ላይ ከኩሽ ህዝብ ጋር የተዋሃዱ) እንደ ሃበሻነታቸው የራሳቸው የሆነ መለያ ታሪክ ነበራቸው። መካድ የማንችለው ትልቁ እውነታ ግን ግሪኮቹ ኢትዮጵያ የሚል ስያሜ የሰጡት ምድር የኩሽ ምድር መሆኑና ኦሮሞ ደግሞ የኩሽ ነገድ ትልቁ ግንድ መሆኑን ነው። ይህ ሰፊ ምድር ደግሞ የዛሬዋን የምንሊክ ኢምፓየር ጨምሮ ኣብዛኛውን የምስራቅና ሰሜን ምስራቅ ኣፍሪቃን የሚያጠቃልል ነው።
ኦሮሞ የኩሽ ነገድ ዋነኛው ግንድ እንደመሆኑ መጠን ማናቸውም የኩሽ ስልጣኔ ኣሻራዎች የራሱ ናቸው። ኦሮሞ ኣሁን የምኒልክ ኢምፓየር ሆና ከተመሰረተችው ኢትዮጵያ ውስጥም ውጭም ሲኖር ነበረ። ሲሻው ሲወጣ ሲሻውም ሲገባ ነው የኖረው። ምክንያቱም መሬቱ ከጥንትም ጀምሮ የነገዱ የኩሽ መሬት ነውና በፈለገው ጊዜ ለመውጣትም ሆነ ለመግባት የማንም ፈቃድ የሚያሻው ኣልነበረምና። ይህ ደግሞ በማናቸውም የኣለም ህዝቦች ታሪክ ውስጥ የሚታወቅ ህዝባዊ ኣኗኗር ነው። ኣለማችን እንደዛሬው የፖለቲካ ድንበሮች ተበጅተው ኣንዱ ኣገር ከሌላው ተለይተው ሳይታወቁ በፊት ህዝቦች እንዳሻቸው ከስፍራ ስፍራ ሲንቀሳቀሱ ኖረዋል። በዚያ ላይ ኦሮሞ ጥንት ከብት ኣርቢ ህዝብ እንደመሆኑ መጠን ለከብቶቹ ግጦሽ ፍለጋ የኣየር ሁኔታው እንደቀናው በስፋት የመንቀሳቀስ ፍላጎት ነበረበት።
በነጻ ህዝቦች ንቀት የተጠናወቱት የነፍጠኛው ልህቃን ማወቅ ያለባቸው ሌላው ትልቁ ነገር እነርሱ የታሪክ ሃብታሞች ሆነው ኦሮሞው የታሪክ ድሃ ኣለመሆኑን ነው። እነርሱ የጥንት ስልጣኔ ባለቤቶች ሆነው ኦሮሞው ስልጣኔ ኣልባ ህዝብ ኣለመሆኑንም ጭምር ማስታወስ ኣለባቸው። የኦሮሞ ህዝብ ስልጣኔ በሁለት መልኩ ይገለጻል። ኣንደኛውና ኣንጋፋው በኩሽ ስልጣኔ ስም ኣለም የሚያውቀው የጥንታዊት ኢትዮጵያ ስልጣኔ ነው። ሁለተኛው ደግሞ ከዚያ ጥንታዊ ዘመን በሁዋላ እንደ ብሄር ይዞት እስከ ዛሬ የዘለቀው ዴሞክራሲያዊው የገዳ ስርኣትና የስነ ከዋክብት ጥናት (Urjii Dhaha) ስልጣኔው ነው። ኦሮሞ በኩሽነቱ የነኑቢያና ኬሜት (ጥንታዊት ግብፅ) የግንባታና የስነፅሁፍ ስልጣኔዎች ባለቤት ነው። እንደ ሁዋለኛው ዘመን ኦሮሞነቱ ደግሞ ኣፍሪቃ ውስጥ በምሳሌነቱ የሚጠቀሰው የዴሞክራሲያዊ ፖለቲካ መገለጫ የሆነው የገዳ ስርኣት ስልጣኔ ባለቤት ነው። ኦሮሞ በገዳ ስርኣቱ መሪውን (ኣባገዳውን) በሰላማዊ መንገድ ሲመርጥና ሲሸኝ፣ ከዚያም በታች ያሉትን ኣስተዳዳሪዎቹን ያላንዳች ደም ጠብታ ሲሾምና ሲሽር ኣለማችን ላይ ህዝቦች በስልጣን ጥም ደም ሲፋሰሱ ኖረዋል። ይህ እንደ ኦሮሞነታችን የምንኮራበት የስልጣኔያችን ዋልታ ሲሆን ለሌሎችም ጎሮቤቶቻችን በምሳሌነቱ የሚጠቀስና እንዲሁም እንደ ጉዲፈቻችን ሁሉ በተውሶ ስራ ላይ መዋል የነበረበት እንጂ በትምክህት መንቁዋሸሽ የሚገባው ባህል ኣይደለም።
ወደተነሳንበት ጉዳይ ስንመለስ የዛሬዋ የምኒልክ ኢምፓየር ኢትዮጵያም የኦሮሞውና የሌላው ኩሽ ህዝብ ሁሉ መፍለቂያና መኖሪያ መሆኗን ልናሰምርበት እንሻለን። እኛ ትምክህተኞቹ የነፍጠኛ ልጆች የኣገሬውን ኣንጋፋ ህዝብ ኦሮሞውን ‘ኣገርህ እዚህ ኣይደለም’ ስላሉት ተረብሸንና ተርበትብተን ‘እናንተም ከደቡብ ኣረቢያ ቀይ ባህርን ኣቁዋርጣችሁ በመምጣት እዚህ የኛ ኩሽ ኣገር ላይ ሰፍራችሁኣልና ለቃችሁ ውጡልን’ እስከ ማለት ኣንሄድም። ትልቁ ጥያቄያችን የትላንትናው የታሪክ ጥያቄ ሳይሆን የዛሬው የፖለቲካ መብት ጥያቄ ነው። የዛሬው የፖለቲካ መብታችን በትላንትናው ታሪካችን ልክ እንዲሰፋልንም ኣንገደድም። ኣብዛኛው የኣለማችን ህዝብ በታሪክ ማንነቱ ላይ ብቻ ተመርኩዞ ኣይደለም የፖለቲካ ኣስተዳደሩን ያዋቀረው።
ይህን ስንል የኣማራ ልህቃን በኣኩይነታቸው ገፍተው ኦሮሞ ኣገሩ እዚህ ኣይደለም የሚል የደንቆሮ ጨዋታ ከቀጠሉበት እኛም ምላሽ ይኖረናል። ኣማራው ማነው፣ ኣገሩስ የት ነው የሚለው ጥያቄ ሊከተል ይችላል። የዚህ ጥያቄ ምላሽ ደግሞ በእጅጉ መልሶ የሚጎዳው ኣሳ ጎርጉዋሪዎቹን የነፍጠኛ ልህቃንንና መከረኛውን የኣማራ ህዝብ ይሆናል። ስለሆነም ዶሮ ጭራ ጭራ… እንዲሉ የምኒልክ ልጆች በገዛ ሰውነታቸው ላይ እባብ ከመጠምጠም እንዲቆጠቡ ኣክመራለሁ።
ያህያ ጀማል

Saturday 22 March 2014

የብርሃንና ሠላም ማተሚያ ቤት መቃጠል

ከተመሰረተ ከ70 ዓመታት በላይ ዕድሜ እንዳስቆጠረ የሚነገርለት በአዲስ አበባ ከተማ ውስጥ የሚገኘው የብርሃንና ሠላም ማተሚያ ቤት ዛሬ ቃጠሎ እንደደረሰበት ወኪላችን ከአዲስ አበባ ዘገበ።


የብርሃንና ሠላም ማተሚያ ቤት የቃጠሎ መንስኤ ለጊዜው በዝርዝር ባይገለፅም በማተሚያ ቤቱ ላይ እሳቱ የተነሳው ከቀኑ 9 ሠዓት ተኩል ግድም እንደሆነ የአዲስ አበባው ወኪላችን ዮሐንስ ገ/እግዚአብሔር ከአካባቢው ነዋሪዎች ያገኘውን መረጃ መሰረት በማድረግ ገልፆልናል። እሳቱ በቁጥጥር ስር መዋሉም ተነግሯል። የብርሃንና ሠላም ማተሚያ ቤት በዕድሜ ጠገብነቱ እና ግዝፈቱ በሀገሪቱ ብቸኛው የማተሚያ ቤት እንደሆነ ይጠቀሳል።
ዮሐንስ ገ/እግዚአብሔር
ማንተጋፍቶት ስለሺ
አርያም ተክሌ

Ethiopia Government Regularly Records Phone Calls – Human Rights Watch


March 22, 2014, NAIROBI, Kenya (AP) — A rights group says that Ethiopia’s government regularly listens to and records the phone calls of opposition activists and journalists using equipment provided by foreign technology companies.
Human Rights Watch said in a report Friday that the foreign equipment aids the Ethiopian government’s surveillance of perceived political opponents inside and outside the country.
The group’s Arvind Ganesan said Ethiopia is using its government-controlled telecom system to silence dissenters. The group says that recorded phone calls with family and friends are often played during abusive interrogations.
Human Rights Watch said most of the monitoring technology is provided by the Chinese firm ZTE. Several European companies have also provided equipment, the group said, including from the U.K., Germany and Italy.
Source: AP

Dispatches: Removing the Bar for Ethiopia

March 22, 2014
hrwOn March 19, the Extractive Industries Transparency Initiative (EITI) decided to admit Ethiopia as a candidate country. With this move, the EITI may have added a member, but it lost its credibility as a good governance initiative.
Bringing together stakeholders from government, industry and civil society organizations, the EITI is supposed to provide incentives for governments to improve transparency in the oil, gas and mining sectors. One key criterion for membership in the group is that governments commit to meaningful participation for civil society on issues related to natural resources. The EITI Standard instructs that, “government must ensure there are no obstacles to civil society and company participation in the process,” including with regard to “relevant laws, regulations, and administrative rules as well as actual practice in implementation of the EITI.”
The logic is simple: publishing data on natural resource issues can only lead to better government decisions if there’s real public scrutiny and an opportunity for civic engagement.
Ethiopia, however, is one of the most repressive countries in the world when it comes to the ability of independent civil society and media to function. Admitting Ethiopia to EITI isn’t just lowering the bar on the need for civil society participation, it’s removing the bar entirely.
The EITI decision is all the more disturbing because in 2010 the EITI Board rightly rejected Ethiopia’s candidacy. It recognized that a draconian 2009 civil society law fundamentally represses civil society in the country, and stated that it would reconsider Ethiopia’s application only when the law was “no longer in place.”
The law prohibits non-governmental organizations from working in human rights and good governance if they receive more than 10 percent of their funds from abroad. As a result, today there are few organizations working on these issues and those that do, self-censor and straddle a knife-edge, always concerned about a potential crackdown. The situation for media freedom is equally dire: Ethiopia has jailed and forced into exile more journalists than anywhere else in Africa, except Eritrea.
Yet, in a complete reversal from its 2010 stance and despite considerable and sometimes bitter debate at a session in Oslo, EITI endorsed Ethiopia’s candidacy.Troublingly, EITI Chair Clare Short claimed that the decision showed “the Board was convinced by the government’s commitment to the EITI’s principles.”
But without a change in Ethiopia’s law, the EITI itself has undermined those principles.
Leslie Lefkow

                                                      
Leslie Lefkow


                                                                                           
     

 By Leslie Lefkow
Human Rights Watch






Friday 14 March 2014

Hjelp oss å redde Etiopia!



- Help us save Ethiopia!
Demonstrated: A 40th century Ethiopians demonstrating in support of their own people in their homeland in Hamar.
Demonstrated: A 40th century Ethiopians demonstrating in support of their own people in their homeland in Hamar.
They competed for the attention of school children celebrating cultural center, but around 40 asylum seekers from Ethiopia provoked a stir in Hamar center Friday morning.
Sverre Frilseth

 Print Send us your tips
Ad

Hamar
Asylum seekers belonging to the Oromo people in Ethiopia, the largest ethnic group in the African country, and they are regarded as indigenous on the Horn of Africa. Around 30 million oromoere lives in Ethiopia, but there are also settlements in Kenya and Somalia.
Today, the Oromo poorly regarded by the government of Ethiopia and among others, Amnesty International and Human Rights Watch have called people a warning about the systematic oppression of the people.
Reports of detention and torture of political leaders, protesters and journalists who place themselves at the head of the Oromo, belongs more to life than rare. "Africa's Kurds" are Oromo called the Western press and media.

Beat Fast

Friday gave a 40-century oromoere sound in unison in Hamar. Through Megaphone and speaking choir were demands for justice, democracy and freedom in their homeland conveyed.
- Norway: Stand up, give your voice to the Oromo, do not support the government's oppression of our people, saying one of the messages of Ethiopians who currently resides respectively Ormseter and Ringsaker refugee reception. They had already obtained Norwegian government permission to conduct the demonstration.

Contrast

It was a colorful crowd as the train away the pedestrian street, with clear, rhythmic shouting and waving posters that drew up demands and desires they have for the future. And most colorful: The flag of red and yellow and green.
Seen from the sidelines was striking contrasts. The weather was not the most welcoming, but even greater distance was between the message of the Oromo who feel oppressed, to the overriding theme of hamar sing the heads of the day:
The opening of the council's new cultural center. The queen and television and culture personalities present and major event at Stortorget and secure everywhere. For we won freedom for a long, long time ago. And retains the page ...

(14.03.2014 at. 4:02 p.m.)

Thursday 6 March 2014

አሟሟታቸው “ሆድ ይፍጀው” የተባለው የኦቦ ዓለማየሁ ቀብር ቅዳሜ ይፈጸማል፤ አስቴርና ሙክታር አስከሬኑን ለማምጣት ባንኮክ ናቸው

(ዘ-ሐበሻ) በባንኮክ በህክምና ሲረዱ ቆይተው ያረፉት የኦሮሚያ ክልል ፕሬዚዳንት ኦቦ ዓለማየሁ አቶምሳ የቀብር ስነ ሥርዓት የፊታችን ቅዳሜ በአዲስ አበባ እንደሚፈጸም ታወቀ። አስከሬናቸውን ከባንኮክ ለማምጣትም ወ/ሮ አስቴር ማሞና አቶ ሙክታር ከድር ባንኮክ የገቡ ሲሆን ዛሬ ምሽት 3 ሰዓት ላይ አዲስ አበባ ይገባሉ ተብሎ ይጠበቃል።



በ45 ዓመታቸው ከዚህ ዓለም በሞት የተለዩት ኦቦ ዓለማየሁ የክልሉን ፕሬዚዳንትነት ከተቀበሉ በኋላ መርዝ እንደተሰጣቸውና ለበርካታ የአልጋ ቁራኛ እንዲሆኑ አድርጓቸው፤ በህክምና ላይ የሰነበቱ ሲሆን አሟሟታቸውም ሆድ ይፍጀው ሆኗል ይላሉ አስተያየት ሰጪዎች።
የአቶ ዓለማየሁ አቶምሳ የቀብር ስነ ሥርዓት የፊታችን ቅዳሜ በቅድስት ስላሴ ቤ/ክ እንደሚፈጸም የታወቀ ሲሆን አስከሬናቸውን ለማምጣትም በምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ማዕረግ የመልካም አስተዳደር ሪፎርም ክላስተር አስተባባሪና የሲቪል ሰርቪስ ሚኒስቴር ሚኒስትር የሆኑት ኦቦ ሙክታር ከድር እና የኦሮሚያ ክልል ፕሬዚዳንት ይሆናሉ ተብሎ የሚጠበቀው ወ/ሮ አስቴር ማሞ ባንኮክ ተጉዘዋል። እነዚህ ሁለት ባልስልጣናትም አስከሬኑን ይዘው ዛሬ አዲስ አበባ ይገባሉ ተብሎ ይጠበቃል።
ይህ በእንዲህ እንዳለ ከባለስልጣኑ ጋር የቀረበ ግንኙነት ነበረን ያሉ ሁለት አስተያየት ሰጪ ጋዜጠኞች በፌስቡክ ገጻቸው ከፕሬዚዳንቱ አሟማት ጀርባ ምስጢር አለ እያሉ ነው። የሁለቱንም አስተያየት ያንብቡት፦
በቅድሚያ የጋዜጠኛ ደመቀ ከበደ አስተያየት
” የ3 ልጆች አባት የነበሩትን አቶ አለማየሁ አቶምሳን የኦሮሚያ ክልል ርዕሰ መስተዳድር ሆነው እንደተሾሙ ሰሞን ለዘገባ አጭር ቃለ መጠይቅ አድርጌላቸው ነበር – አዳማ ላይ፡፡ ሰውየው በሙስናና ሙሰኞች ላይ የመረረ አቋማቸውን ሲነግሩኝ ‹‹ቆራጥነት›› ባዘለ ቃና ነበር፡፡
ይህንን በተግባርም አሳይተዋል ብዬ አምናለሁ፡፡
ግን ብዙ ሳይቆዩ መታመማቸው ተሰማ፤ የህመማቸው ምክንያቱ ደግሞ የሌባ ጠላት መሆናቸው ነው ተባለ፡፡ ‹‹ድሮስ አሰለጥ ሌባ መች ለጠላቱ ይተኛል›› … በሚል ነገሩ ወዲህና ወዲያ ተነዛ፡፡ ተጨባጭና ሁነኛ መልስ ግን ያገኘ አላጋጠመኝም፡፡
እንደ ጥላሁንን ገሰሰ ሆድ ይፍጀው ሁላችንም የህመማቸው ምክንያቱን ብንጠብቅም ‹‹በየጊዜው ደም እየቀየሩ ነው ከህመማቸው የሚያገግሙት›› ከሚል ወሬ በቀር ሀቁን ይሄ ነው ያለ የለም፡፡ ከእሳቸው አንደበትም የተሰማ ነገር የለም – እስከማውቀው ድረስ፡፡
ይህ በእንጥልጥል እንዳለ ሰሞኑን ስልጣናቸውን በህመም መልቀቃቸውን ሰምተን ብዙ ሳንቆይ ዛሬ ደግሞ ‹‹ከዚህ ዓለም መለየታቸውን›› አደመጥን፡፡ አቶ ሙክታር ከድርና ወ/ሮ አስቴር ማሞ እየታከሙ ከነበረበት ‹‹ባንኮክ›› ከቤተሰባቸው ጋር ‹‹አስከሬናቸውን›› ሊያመጡ እዚያው መገኘታቸውም ተነግሯል፡፡
ያሳዝናል፡፡ በዚህ ዕድሜ መሞታቸው ብቻ ሳይሆን የአገርን ሙስና ‹‹አፈር ድሜ›› ለማብላት ቁርጠኛነትን ‹‹ለሌሎቹ ሳያሳዩልን›› ሞት ስለቀደማቸው ያሳዝናል፡፡
ከአቶ አለማየሁ አቶምሳ ያጣነው አለ – የሌባ አዳኝ መሆንን!
!”
የሰንደቅ ጋዜጣ አዘጋጅ ፍሬው አበበ በበኩሉ እንዲህ ብሏል፦
“የቀድሞ የኦሮሚያ ክልል ፕሬዚደንት የአቶ አለማየሁ አቶምሳ ዜና ዕረፍት ስሰማ እጅግ አዝኛለሁ፡፡ አቶ አለማየሁን በአካል የማውቃቸው በ2002 ዓ.ም ወሩን በማላስታውሰው ጊዜ ለስራ የቢሮአቸውን ደጃፍ በረገጥኩበት ወቅት ነበር፡፤ ያኔ አቶ አለማየሁ የማስታወቂያ ቢሮ ኃላፊ ነበሩ፡፡ ለቀጠሮ በቢሮአቸው ድንገት ስገኝ ምናልባት ቢያናግሩኝ በሚል ቀቢጸ ተስፋ በመሰነቅ ነበር፡፡ በአጋጣሚ አቶ አለማየሁ በቢሮአቸው ውስጥ ነበሩና እንድገባ ፈቅደውልኝ በጨዋ ደንብ ከመቀመጫቸው ተነስተው በአክብሮት ያደረጉልኝ አቀባበል ምናለ ሌሎቹም ሹማምንት ከሳቸው ቢማሩ የሚያሰኝ ዓይነት ነበር፡፡ ተግባቢ ሰው በመሆናቸው ከሄድኩበት ርዕሰ ጉዳይ ውጪ ስለግሉ ፕሬስ ላይ ላዩን ለመነጋገር ችለናል፡፡ በዚህ አጋጣሚ አቶ አለማየሁ የግሉ ፕሬስ መኖርና መጠናከር ለስርኣቱ ግንባታ ወሳኝ ነው ብለው የሚያምኑ ቀና ሰው መሆናቸውን ለመረዳት ችያለሁ፡፡ በወቅቱ ፍጹም ጤነኛ እና የተረጋጉ፣ ትልቅ የመሪነት ካሪዝማ ያላቸው ሰው እንደሆኑ በአጋጣሚ መታዘብ ችዬ ነበር፡፡
እናም የክልሉ ፕሬዚደንትና የኦህዴድ ሊቀመንበር ሆነው ከተሾሙ ጥቂት ወራት ግዜ በኃላ ከባድ ሕመም ላይ መውደቃቸው በእርግጥም ከጀርባቸው የተሸረበባቸው ተንኮል (ሴራ) ስለመኖሩ በብርቱ እንድንጠረጥር በር የሚከፍት ነው፡፡ ነፍስ ይማር!!”

እውነት እየቆየ መውጣቱ አይቀርም፤ የዘ-ሐበሻ አንባቢዎችስ ምን ትላላችሁ?

(ሰበር ዜና) መርዝ ተሰጥቷቸዋል የተባሉት የኦሮሚያ ክልል ፕሬዚዳንት ኦቦ ዓለማየሁ አቶምሳ አረፉ

ለህክምና ብዙ ገንዘብ ወጣባቸው በሚል ሕገወጥ በሆነ መንገድ ከስልጣናቸው እርሳቸው ባላወቁበት በፈቃዳቸው እንደለቀቁ ተደርጎ የተነገረባቸው የኦሮሚያው ክልል ፕረዚዳንት ኦቦ አለማየሁ አቶምሳ በተሰጣቸው የተመረዘ ምግብ ምክንያት የጀመራቸው በሽታ በከፍተኛ ሁኔታ ጸንቶ በተደጋጋሚ በተለያዩ ሃገራት ህክምናቸውን ሲከታተሉ የቆዩ ሲሆን ዛሬ ግን በባንኮክ ታይላድ ለህክምና በሄዱበት ሆስፒታል ሕይወታቸው አልፏል።
በ45 ዓመታቸው በታይላንድ ባንኮክ ሕይወታቸው ያለፈው ኦቦ ዓለማየሁ አቶምሳ በምን ምክንያት የተመረዘ ምግብ እንደተሰጣቸው ባይታወቅም ከርሳቸው ጋር ምግቡን በልቶ የነበረ ግለሰብም እስካሁን በሞት አፋፍ ላይ እንደሚገኝ ለዘ-ሐበሻ የደረሱ መረጃዎች ያመለክታሉ። ለዘ-ሐበሻ ቅርብ የሆኑ የኦነግ የመረጃ ምንጮች “ኦህዴድን የድሮው ኦህዴድ እንዳይሆን ሊያደርጉ የሚችሉ ሰው ስላልነበሩ በሕወሓቶች መርዝ እንዲሰጣቸው ተደርጓል” የሚል አመለካከት ያላቸው መሆኑን ገልጸው ሕወሓት አቶ ዓለማየሁን ቀጠፋቸው ሲሉ ይተቻሉ”፡
ከየካቲት ወር መጀመሪያ ጀምሮ በባንኮክ ህክምና ላይ የከረሙት በምስራቅ ወለጋ ቢሎ ቦሼ ወረዳ ከአባታቸው አቶ አቶምሳ ሚጃ እና ከእናታቸው ወይዘሮ አየለች ብሩ በ1961 ዓ.ም ተወለዱት አቶ ዓለማየሁ አቶምሳ ሕይወታቸው በእንዲህ ያለ ሴራ ማረፉ በኢሕአዴጎች መካከል አለመተማመንን ሊፈጥር እንደሚችል የተለያዩ የፖለቲካ ታዛቢዎች እየገለጹ ነው።


የኦህዴድ/ኢህአዴግ ማዕከላዊ ኮሚቴ ፅህፈት ቤት ዛሬ ባወጣው መግለጫ አቶ ዓለማየሁን “ላለፉት 24 ዓመታት የኦሮሞ ህዝብ እና መላው የአገሪቱ ህዝቦች ዛሬ ለደረሱበት የሰላም፣ የዴሞክራሲና የልማት ተጠቃሚነት እንዲበቁ በቁርጠኝነት የታገሉ ነባር ታጋይ ነበሩ” ካለ በኋላ በ1981 ዓመተ ምህረት የደርግን ስርዓት ለመገርሰስ ሲካሄድ የነበረውን የትጥቅ ትግል መቀላቀላቸውን፣ ከ1988 እስከ 1994 ድረስም የኦህዴድ ማዕከላዊ ፅህፈት ቤት እና የድርጅቱ የፖለቲካ ዘርፍ ኃላፊ በመሆን ማገልገላቸውን፣ ከ2002 ዓመተ ምህረት ጀምሮ የኦህዴድ ሊቀመንበር ሆነ ከ2003 ዓ.ም ጀምሮ ደግሞ የኦሮሚያ ብሄራዊ ክልላዊ መንግስት ርዕሰ መስተዳድር መሆናቸውን ጠቅሷል። ሆኖም ግን ድርጅቱ እንደተጠበቀው አቶ አለማየሁ በተመረዘ ምግብ መሞታቸውን ከሴራው በስተጀርባ ማን እንዳለ ያስቀመጠው ነገር አለመኖሩን የዘ-ሐበሻ ዘጋቢዎች ጠቁመዋል።
በሌላ በኩል ለዘ-ሐበሻ በደረሱ መረጃዎች ቀጣዩ የኦሮሚያ ክልል ፕሬዚዳንት ወ/ሮ አስቴር ማሞ ይሆናሉ የሚለው ግምት ሚዛን እየደፋ ነው።

Monday 3 March 2014

Migrant dies in Saudi detention centre riot


Saudi campaign to expel undocumented foreign workers comes after decades of lax immigration enforcement [EPA]
Saudi campaign to expel undocumented foreign workers comes after decades of lax immigration enforcement [EPA]
March 3, 2014 (Aljazeera) — Officials say that one was killed and nine others injured when chaos broke out at a deportation centre in Jeddah.
A migrant has died and nine others have been wounded in a stampede during a riot at a Saudi detention centre in the west of the kingdom, police have said.
Police said on Monday that they had attempted to restore calm on Sunday evening at al-Shumaisi detention centre in the Red Sea city of Jeddah where undocumented migrants of various nationalities are held pending deportation.
Detainees “tried to cause chaos… resulting in damages to the centre,” Mecca police spokesman Commander Ati al-Qurashi told AFP news agency.
He did not elaborate on the nature of the disturbances but said that police “had to intervene” and that a migrant was killed and nine others wounded in a “stampede”.
The spokesman did not provide further details on the nationalities of the casualties, the number of migrants held at the deportation centre, or the progress made in their deportation procedures.
The Saudi migrants sweep has sparked violence before. In November, at least one Ethiopian and a Sudanese were killed in clashes between migrant workers protesting the crackdown and vigilante Saudis in the capital Riyadh. Similar clashes also broke out in Jeddah when police searched the area for migrants.
The deportations are part of a Saudi campaign to expel undocumented foreign workers after decades of lax immigration enforcement allowed migrants to take many low-wage jobs that the kingdom’s own citizens shunned. Saudi authorities, grappling with growing unemployment, now want those jobs for the kingdom’s citizens.
Police have been cracking down on undocumented migrants since the expiration in early November of a seven-month amnesty during which they had to regularise their status or leave the country.
Nearly a million migrants from various countries took advantage of the amnesty to leave voluntarily, while another four million were able to find employers to sponsor them, a legal requirement in Saudi Arabia and other Gulf states.
The Saudi government says it has deported more than a quarter-million migrants since the government began enforcing its crackdown.
Around 170,000 of those are Ethiopians, most of whom never acquired visas, often taking perilous boat journeys across the Gulf of Aden to Yemen from where they cross illegally into the kingdom with the help of smugglers.
Human Rights Watch has criticised the conditions of detainees awaiting deportation in the kingdom. The rights group last month said more than 12,000 Somali migrants were held under “appalling conditions” before they were deported from Saudi Arabia.
The majority of foreign workers in the kingdom are from India, Pakistan, Bangladesh, Indonesia and the Philippines, as well as Egypt and Yemen.
Source: Aljazeera

ከጭሮ ከተማ ቃሊቲ ማረሚያ ቤት እንዲዘዋወሩ ከተደረጉት ታሳሪዎች መካክለ ሼህ ሃሰን በቂ ህክምና ባለማግኘታቸው ሂወታቸው ማለፉን ምንጮች አስታወቁ

March 2, 2014

በኦሮሚያ ክልል በምዕራብ ሃረርጌ በጭሮ ከተማ በሚገኙ ከተለያዩ ወረዳዎች በፖሊስ ተይዘው በጭሮ ከተማ ማረሚያ ቤት ለረጅም ጊዜ ታስረው ለህክምና ወደ ቃሊቲ ማረሚያ ቤት እንዲዘዋወሩ ከተደረጉት ታሳሪዎች መካክለ ሼህ ሃሰን በቂ ህክምና ባለማግኘታቸው ሂወታቸው ማለፉን ምንጮች አስታወቁ፡፡
በጭሮ ከተማ ከተለያዩ ወረዳዎች በጭሮ ከተማ ማረሚያ ቤት ታስረው ባደረባቸው ከፍተ|ኛ ህመም ምክንያት ማረሚ|ያ ቤቱ ከአንድ አመት በፊት ወደ ፌደራል ማረሚያ ቤት ወደሆነው ቃሊቲ ማረሚ|ያ ቤት ሪፈር በመፃፍ ወደ አዲስ አበባ ሄደው እንዲታከሙ ለማድረግ ሞክሮ ነበር፡፤ ሆኖም ታሳሪዎቹ በቃሊቲ ማረሚያ ቤት በዞን 3 ታስረው የሚገኙ ሲሆን ምንም የረባ ህክምና ሳያገኙ በከፍተኛ ህመም እየተሰቃዩ እንደሚገኙ ምንጮች አስታውቀዋል፤፤
ከምዕራብ ሃረርጌ ጭሮ ከተማ ማረሚያ ቤት ወደ ቃሊቲ ማረሚያ ቤት ከአመት በፊት የተዘዋወሩት ታሳሪዎቹ ስም ዝርዝር እንደሚከተለው ይቀርባል
1. መሐመድ ሐሰን አሊዩ በምዕራብ ሀርርጌ ዞን ጭሮ ከተማ ደባቢስቶ ወረዳ ቡሌ ኢሉ ቀበሌ
2. መሃመድ አህመድ በምዕራብ ሀርርጌ ዞን ጭሮ ከተማ ደባቢስቶ ወረዳ ቡሌ ኢሉ ቀበሌ
3. ሼህ ሀሰን በምዕራብ ሀረርጌ ዳሮ ለቦ ወረዳ ገለሞተራ ቀበሌ
4. ከተማ ጸጋዬ መገናኛው በምዕራብ ሃረርጌ መቻሬ ወይም ገመቺስ ወረዳ ሽሬ ቡሉ ቀበሌ
5. ከተማ ለማ ኢሾ በምዕራብ ሃረርጌ መቻሬ ወይም ገመቺስ ሽሬ ቡሉ ቀበሌ
6. ዘውዱ ታሪኩ እንደሻው በምዕራብ ሃረርጌ ዳርጌ ሳውሮ ወረዳ ቀበሌ 34 ነዋሪ የነበሩ መሆናቸው ታውቋል፡፡
ከላይ ከተዘረዘሩት በቃሊቲ ማረሚያ ቤት በዞን 3 ታስረው ከሚገኙት ታሳሪዎች መካከል በምዕራብ ሃረርጌ የጭሮ ከተማ የደባቢስቶ ወረዳ ቡሌ ኢሉ ቀበሌ ነዋሪ የነበሩት ሼህ ሃሰን በማረሚያ ቤቱ በቂ ህክምና እንዳያገኙ በመደረጋቸው በየካቲት 15/2006 ሂወታቸው ማለፉን የማረሚያ ቤቱ ምንጮች አስታውቀዋል፡፡
ሼህ ሃሰን ከጭሮ ከተማ ማረሚያ ቤት በቂ ህክምና እንዲያገኙ በሚል አብረዋቸው ከታሰሩ ሌሎች ታሳሪዎች ጋር ወደ አዲስ አበባ ቃሊቲ ማረሚያ ቤት ቢዘዋወሩም ማረሚ|ያ ቤቱ ተገቢ እና በቂ ህክምና እንዳያገኙ በማድረጉ ከዚህ አለም በሞት ሊለዩ እንደቻሉ ታውቋል፡፡ የሼህ ሀሰን ቤተሰቦችም ሊያገኟቸው አለመቻላቸውን የማረሚያ ቤቱ ምንጮች ገልፀዋል፡፡
በተመሳሳይም ሁኔታ ሌላኛው በምዕራብ ሀርርጌ ዞን ጭሮ ከተማ ደባቢስቶ ወረዳ ቡሌ ኢሉ ቀበሌ ነዋሪ የነበረው እና የዞን 3 ታሳሪ የሆነው .መሐመድ ሐሰን አሊዩ በቂ ህክምና ባለማግኘቱ በማረሚያ ቤቱ ውስጥ በሞት አፋፍ ላይ እንደሚገኝ ምንጮች አስታውቀዋል፡፡
በኢትዬጲያ በሚገኙ ማረሚያ ቤቶች ታስረው የሚገኙ ዜጎች ከጊዜ ወደ ጊዜ በህክምና እጦት ምክንያት ሂወታቸው በስቃይ የሚያልፉ ታሳሪዎች ቁጥር እየጨመረ መምጣቱ እየተሰማ ሲሆን የማረሚያ ቤቶቹ አስተዳደሮች ለሰው ልጅ ሂወት ክብር በመንፈግ ይህን ችግር ከመቅረፍ ይልቅ የፖለቲካ መቅጫ ዘዴ አድርገው መቀጠላቸው ታውቋል፡፡
ከዚህ ቀደም በቂሊንጦ ማረሚያ ቤትም ወረርሽኝ ገብቶ ጋዜጠኛ ዩሱፍ ጌታቸውን |ጨምሮ በርካታ የማረሚያ ቤቱ ታሳሪዎች ለህመም ተጋልጠው እንደነበር ይታወሳል፡፤ በማረሚያ ቤቱ ባለው የንፅህና ጉድለት እና መጥፎ ሽታም ኮሚቴዎቻችንንም ጨምሮ ለከፍተኛ የሳይነስ እና ተዛማጅ በሽታዎች ተጋላጭ እንዲሆኑ እንዳደረጋቸው ይታወቃል፡፡
ወደ አኼራ የሄዱትን ሼህ ሀሰንን አላህ ማረፊያቸውን በጀነት ያድርግላቸው!!
በመላው ሃገሪቱ ታስረው የሚገኙ ታሳሪዎችን አላህ በራህመቱ ይጠብቃቸው!!!
አሚን!!!
Source: Dargaggotta Oromoo Oslo