Saturday 21 December 2013

ገደብ ያጣው ግፍና የጭቆና መረብ በኦሮሞ ትውልድ ላይ

By Getinet Dinkayehu
የወያኔ እነቅስቃሴ በኦሮሞ ህዝብና በኦሮሞ ድርጅታዊ እነቅስቃሴ ላይ ያላቛረጠ ጭቆናና የመብት ረገጣ በማድረግ የተለያዩ ኢ-ዲሞክራሳዊ የመብት ጥሰቶችን እየፈፀመ ይገኛል:: ለዚህም ስትራተጂዎችን በመንደፍና የነደፈውን በመተግበር ዛሬ አለም የሰዉ ልጆችን መብት ከመጠበቅ አልፎ የእንስሳትን መብት እየጠበቀ ባላበት ዘመን ላይ የኦሮሞ ልጆችን መብት በማሳጣት ከአለም ሚዲያዎች በመሰወር እንዲሁም በግልጽ እየረገጠ ይሄው ድፍን 22 አመት አለፈው። የአለም መንግስታት ወያኔ በላዩ በሽፋን የያዘውን ዲሞክራሲ የሚል የውሰጥ መርዝና ገዳይ ስራውን በተለያየ መንገድ ቢገንዘቡትም የኦሮሞ ህዝብ ችግር ግን ሰሚ ያጣ ይመሰላል። የአንድ ብሄር ዝርያዎች ብቻ በስልጣን ላይ መቀመጥና መግዛት የለሎች ብሄሮች በህይወትና በሞት መሃል ተገዝቶ መኖር የኦሮሞ ህዝቦች ደግሞ እያጣጣሩ እንኴን እንዳይኖሩ በሚደረግበትና የወያኔ የእስር ቤት ቋንቌ ኦሮምኛ በሆነበት በዚህ ወቅት ዲሞክራሳዊ አስትዳድር አለን ብለው በዉሸት ህዝብንና አለምን ለማታለል መሞከር ገዢው ወያኔ በፍፁም ዲሞክራሲን በስም እንጂ በተግባር የማያውቅ መሆኑን ለተመለከተው ሰው ሁሉ ግልፅ ነው።
በየትኛው ዲሞክራሲ ያለበት ሀገር ላይ አንድ መንግስት ለ22 ተከታታይ ዓመታት በግፍ እንደሚገዛም እኔ አላውቅም ።
ባለፉት ረጅም ዘመናት ከእግዚአብሔር የተሰጠን ስልጣን ነው እያሉ የኦሮሞ ልጆችን በግፍ እንደ በግ ስያርዱ፣ስያስሩ፣ሲገርፉና በቆሻሻ እንደተነካ እንጨት ከእግዚአብሔር የተሰጠውን ማንነቱን ስያንቌሽሹ በነበሩት አፄዎች ስንገዛ ነበር ። ያ ሁሉ በሚሊዮኖች የሚቆጠሩ የኦሮሞ ልጆች ላይ የደረሰው የዘር ማጥፋት ወንጀል ጭራሽ እንደ ፅድቅና ቅድስና ተቆጥሮላቸው ሰሞኑን በቤተ ክርስታናቸው ውስጥ ዛሬም የዱሮውን ለመመለስ ደፋ ቀና እያሉ ባሉት ክፋትን በተሞሉ ልጆቻቸው 100ኛ አመታቸው ሲዘከርላቸው ስመለከትና የብዙ ሺ የኦሮሞ ልጆችን ደም ስያፈስ የነበረው የወያኔ ክፉ መሪ ዛሬም እንደ ትልቅ ጀብዱና ታላቅ መሪ ታይቶ በዚች ውሽት በሞላባት አለም ላይ ሲወደስ ሳይ የአለም ክፉነት ገደብ እንደለለው ያሳየኛል።ይሄንን ሁሉ ግፍ ከኦሮሞ ህዝብ የዋህነት ጋር ሳነፃፅረው በጣም ያሳዝናል። የዋህነታችን አልጠቀመንም ጐድቶናል፣ በድሎናል ።
የአሁኑ የወያኔ የዉስጥ ገዳይ የአገዛዝ ስልት ደግሞ የሰሚ ያለህ ብሎ የሚያስጮህ፣የሚያስመርር ጉዳይ ነው። በአሁኑ ወቅትም በሃገር ዉስጥ በኦሮሞ ወጣቶች የሚደረግ የነፃነት ትግል እየጠነከረ በሚሄድበት ግዜ ሁሉ ወያኔ መነሻው የኦሮሞ ነፃ አውጪ ግንባር ነው በሚል በተለመደው የሂሳብ ስሌቱ የኦሮሞ ልጆችን እየገደለና እያፈሰ እስር ቤት ከማጎር አልፎ የኦሮሞን ህዝብ የነፃነት ጉዞ ለማዳከም  የተለያዩ መርዛማ ዘዴዎችን በመጠቀም የኦሮሞ ህዝብንና የነፃነት ትግልን ለመለያየት ብሎ ለሰው ልጆች የማየገባን የጭካኔ ግፍ እየተገበረ ነው ።
የዛሬውን አያድርገዉና የኦነግ ድርጅት ወያኔን የትግል ስልትና አካሄድ በማስተማር እንዲሁም ደርግን በመጣል ረገድ ከፍተኛውን ሚና የተጫወተ ቢሆንም ከትግል ይዞት የገባውን አጀንዳ እንዳይፈጽም መጠነ ሰፊ ተግዳሮቶች በወያኔ መንግስት የገጠመው ከመሆኑም ባሻገር የኦሮሞን ህዝብ ለማታለል በወያኔ ሳምባ በሚተነፍስና የወያኔን ጭምብል ባጠለቀው የኦህዴድ ድርጅት የኦሮሞን ትውልድ በእጅ አዙር ለመግዛት ስልታዊ የሆነ የአገዛዝ መረቡን በኦሮሞ ህዝብ ላይ ዘርግቶ በደሎቹን ለመሸፈን  የኦሮሞን ህዝብ የሚያስተዳድረው ኦሮሞ ነው በማለት ይስበክ እንጂ ኦሮሞን እያስተዳደረ ያለው ኦሮሞ እንዳይደለ እንዃን ህዝቡ የአለም ህዝብ ያውቀዋል :: በቅርቡ ደግሞ ድምበር በመሻገር ከጎሮበት ሃገራት ጋር ጠላቴ ነው ሲል ከነበረው ከኤርትራ መንግስት ጭምር ድርድር ለማረግ ፕሮፖጋንዳ መንዛት መጀመሩ ጉዞው ወደት እንደ ሆነ ለመረዳት አያስቸግረንም።
ኤረ ለመሆኑ የኦሮሞ እስትዳደር ለኦሮሞ ያሰፈልጋል ብሎ ወያኔ ካመነበት ለምንድን ነው ኦነግን በጥይት የሚያሳድደው ?
በርግጥ ኦነግ በኦሮሞ ህዝብ ዘንድ ድርጅት ብቻ ሳይሆን የኦሮሞ ህዝብ የማንነት መገለጫ መሆኑን ወያኔ ጠንቅቆ ያውቀዋል። ለዝህም ነው በጥይት ኦነግን ማሳደድ የኦሮሞ ህዝብን ማንነት አጥፍቶ ያለገደብ በጨለማ ለመምራት ብቸኛው ምቹ መንገድ እንደ ሆነ በማሰብ ያለ እረፍት እየሰራበት ያለው።
ለዚህም የሃገሩን ሰርዶ በሃገሩ በሬ እንደሚባለዉ ተረት ወያኔ በስሩ ባቋቋመዉ በራሱ ሳምባ በሚተነፍስ የኦህዴድ ድርጅትን በመጠቀም የኦሮሞ ህዝብን የማንነት ስሜት ለማጥፋትና ሀገሩን ለመበዝበዝ ህዝቡን በመከፋፈል፣በማጨፋጨፍ፣የኦሮሞን የነጻነት ትግል እንቅስቃሴዎች ለማፈንና ወደ ኋላ ለማስቀረት ከሊስትሮ ጀምሮ እስከ ላይ ድረስ በጥቅም ፈረስ ላይ ሆነው በሚጋልቡት ደህንነቶችንና አጨብጫቢዎችን በማሰማራት ከፍተኛ ጭቆናና በደል እያደረሰ እንዲቀጥል ምቹ ከለላ የሆነለት ይመስላል:: ዛሬ የኦሮሞ ህዝብ ጥያቄ እንደ ኦህዴድ ባለው የውሸትና ሆድ አደር ስብስብ ተመልሿል ብሎ ወያኔ በመስበክ የኦሮሞን ህዝብ በሙሉ ያታለለ መስሎታል። እዚህ ጋ ሳልናገር የማላልፈው ነገር ቢኖር ግን የኦሮሞ ህዝብ ጥያቀ በቋንቋው መናገር ብቻ አይደለም ። በዚህ ብቻ 40 ሚሊዮን ህዝን ለማታለል መሞከር ሞኝነት ነው። ስለዚህ የኦሮሞ ህዝብ ጥያቄ እስኪመለስና ኦሮሞ በራሱ ሀገር ላይ የባለበትነት መበቱን እስኪጎናፀፍ ድረስ ወያኔ ለግዜው እንዲሁ ይለፋል እንጂ የኦሮሞን የነፃነት ትግል ለማዳከምም ሆነ ለማጥፋት መላውን የኦሮሞን ህዝብ ካልጨረሰ በቀር መቼም እንደማይሳካለት ነው። አንድ ቀን እሮሞ ነፃ መውጣቱ ስለማይቀር ነፃነቱን ያገኜ ቀን ግን ላደረሱት በደለ ወንጀለኞቹን ከጥቅም አጨብጫቢዎቻቸው ጭምር በፍርድ እንደሚፋረዳቸው አንዳች ጥርጥር የለዉም::
የወያኔ መንግስት በየወቅቱ እንደ እስስት እራሱን እየቀያየረ የሚኖር ከመሆኑም በተጨማሪ ጠዋት የተናገረዉን ማታ መድገም በማይችሉ የውሸት ቛጥ በሆኑ ካድረዎች የኦሮሞን ህዝብ እየዘረፈ ለመግዛት ፣ በመግደል፣ በማሰርና የኑሮ ዋስትናን በማሳጣት ከአገር እንዲሰደድ ለማረግ ስልቱን በመቀያየር እየሰራ መሆኑን መገንዘብ ያለብን ይመስለኛል።
የወያኔ እስስታዊ ባህሪና የውስጥ ገዳይ ስልቶችን በኦሮሞ ላይ የሚተገብርባቸው መነገዶች
በግልፅ የውሸት ሽፋን ያለውን አፋኝ ህግ በማውጣት
የሃገሪቷን 6% የማይሞላው የህወሓት የማፍያ ቡድን አብዛኛውን ዋና ዋና የአገሪቷን ሥልጣኖች በሙሉ በራሱ ቁጥጥር ውስጥ በማስገባት የፖለቲካ የኢኮኖሚና የማህበራዊ ዘርፎችን ጭምር በሞኖፖሊ በመቆጣጠር መሪውን ይዞ ወደፈለገበት እያሽከረከከረ ከመገኘቱ ባሻገር የራሱን የስልጣን እድሜ ለማራዘም ሲል ሰፊው የኦሮሞ ህዝብ ላይ ባነጣጠረ መልኩ አፉን ለማፈን ህጎችን እንደፈለገ በማውጣትና እንደፈለገ በመተግበር ላይ ነው ።
ከእነዚህም መካከል በትልቁ በአለም ሚዲያዎች የሚታወቀውን ወያኔ በግልፅ በህገመንግስቱ ላይ በቅርብ ያወጣዉ የአሸባሪነት ህግን የሚመለከት ይሆናል። አሁንም ይህን ሃሳብ ሳነሳ የሰሚ ያለህ ብሎ የሚያስጮህ ነዉ።
በአለም ላይ የፀረ አሸባሪነት ህግ የወጣው በዋናነት ንፁሃን (innocent) ህዝቦችን ከሽብር ለመከላከል ሲሆን የፀረ አሸባሪነት ህግ በወያኔ የወጣበት ዋናው ምክንያት ግን ንፁሀን(innocent) የሆኑትን የኦሮሞ ልጆችንና ለሎችንም ለማሸበር ታስቦ የወጣ መሆኑ ግልፅ ነው።በለላ አነጋገር አለም የፀረ አሸባሪነትን ህግ የምትጠቀመው ንፁሃን ህዝቦች እንዳይሸበሩ ለመከላከል ሲሆን ወያኔ ግን ንጹሃን ህዝቦችን እራሱ እያሸበረበት ነው።
የኦሮሞ ህዝብ በየትኛዉ ስራዉ ነው በአለም ህዝብ የሚታወቀዉ ? በአሸባሪነት? ለመብትና ለነፃነት መታገል፤በሀገራችን ላይ የባለበትነት መብት ይሰጠን ማለት፤የኦሮሞ ህዝብ መተዳደር ያለበት በኦሮሞ ነው ማለት፤ሀብትና ንብረታችንን አትስረቁን አትበዝብዙን ማለት አሸባሪነት የሚያስብል ከሆነ እንግያውስ አለም ሁሉ አሸባሪ ናት ማለት ነው:: ለነነገሩ አለም ባታዳላ ኖሮ የኦሮሞ ህዝብ እስከዛሬ ድረስ በባርነት ስር ባልኖረና ነበር:: የወያኔ መንግስት የኦሮሞን ህዝብ ለማሰርና ለመግደል እንዲሁም ከሃገር ለማባረር በቀን እንዲህ አይነት ህግ አዉጥቶ ኢየሰራበት መገኘቱን ስመለከት ለካ አለም አባት የላትም እላለው::በርግጥም አባት የላትም።
ትንሽ አሻሮ ይዞ ወደ ቆሎ ጠጋ የሚባለዉን የተረት አባባል በመያዝ ወያኔ በአለም ላይ የወጣዉን የአሸባሪነት ህግ በተሳሳተ መንገድ በመጠቀም አንድን ብሄር(ኦሮሞን) ለማጥፋት ሲጠቀም የአለም መንግስታትና የሰባዊ መብት ተከራካሪ ድርጅቶች ዝምታን መምረጥ በኦሮሞ ላይ የሚደርሰውን በደልና ጭቆና የከፋ እያደረገ ይገኛል:: የአንድ አምባገነን መንግስት የዘር ማጥፋት ህግ በማዉጣት የሰዉን ልጅ ያለገደብ መጨፍጨፍ መች ነግቶ በማን ይጠየቅ ይሆን?
በሀገር ውስጥ ከምያደርሱት በደል በተጨማሪ የእነሱን የግፍ አገዛዝ በመሸሽ ወደ ጎሮበት ሀገራት ሄደው በፖለቲካ ጥገኝነት በUNHCR ተመዝግበው የሚኖሩትን የኦሮሞ ልጆች እንኳ በሰላም እንዳይኖሩ ባሉበት በማሳደድ የፀረ አሸባሪነት ህግን በሽፋን በመጠቀም ከጎሮበት መንግስታት ጋር ስምምነት ፈጥረው እጅ እግር አስረው በመመለስ የእድሜ ልክና የሞት ቅጣት ቀማሽ እንዲሆኑ እየተደረገ መሆኑ የዚህን ህግ አስከፊነትን ያመለክታል።እንደ ምሳሌነት ብናነሳ በቅርቡ ወጣት እንጅነሮች ተስፋሁን ጨመዳና መስፍን አበበ ከኬኒያ የተያዘበት ዜደና በወያኔ እስር ቤት ውስጥ የደረሰባቸው አሰቃቂ ግድያ መላውን የኦሮሞ ህዝብ ያስለቀሰ ጉዳይ ነው።በአሁኑ ግዜም በዚህ የወያኔ ፀረ ሽብር ህግ ምክንያት በጎሮበት ሀገራት በፖለቲካ ጥገኝነት የሚኖሩ የኦሮሞ ልጆች ተሰሚነት አያጡ በስጋት ውስጥ እየኖሩ መሆኑን በተደጋጋሚ እየሰማን ነው።
የሽፍተኝነት ባህሪን በመላበስና በመግደል
የወያኔ መንግስት ፀረ ህዝብ ፤ፀረ ዲሞክራሲ ፤ፀረ ኦሮሞ ነው ብየ ብገልጽ የአደባባይ ሃቅ ነው። ይህንን ለማለት የቻልኩበት ምከንያት ወያኔ ደርግን ለመጣል የተነሳሳውና ወደ ጫካ ገብቶ በሽፍተኝነት ጀምሮ ለድል የበቃ መንግስት ሲሆን ደርግ በአደባባይ ነጭ ሽብር ቀይ ሽብር እያለ የንፁሀንን ደም ስያፈስ ወያኔ በሚድያዎቹ ሲኮንንና ሲከስ ስለነበረ እራሱን ከደርግ ሥርዓት የተሻለ አድርጎ የሚቀርብ ይመስል ነበር:: ነገር ግን ዛሬ የደርግ ጭፍጨፋ መልኩን ቀየረ እንጅ በሀገሪቱ ላይ በወያኔ እየተደረገ ያለው በደል ከደርግ የባሰ እንጂ የሚያንስ አይደለም ።
በብዙ ሺ የሚቆጠሩ የኦነግ ሰራዊቶችን በሰላማዊ መንገድ በድርድር በነበሩበት ወቅት ትጥቅ አስፈትቶ በካምፕ ዉስጥ በማስገባት ትጥቅ የፈታን ህዝብ በታንክና በከባድ መሳሪያ መጨፍጨፉ አሰቃቂ የአደባባይ ግድያውን የምያመለክት ሲሆን በተጨማሪም በካድረዎቹና በደህንነቶቹ ጥይት በየግዘው በአደባባይ የሚገደሉትን የኦሮሞ ልጆች ደግሞ ቤት ይቁጠራቸ። አሁን አሁን ደግሞ ወያኔ የሰዉን ልጆች ለማጥፋት የሚጠቀመው መጠነ ሰፊ ስልቶች ሲኖሩት እያራመድኩ ያለሁት ዲሞክራሲ ነው ብሎ ለመስበክ እንዲመቸው በተወሰነ መልኩ በአደባባይ የሰዉን ልጆች ከማጥፋት ሲልቱን በመቀየር የሽፍተኝነት ባህሪውን አሁንም በንፁሃን የኦሮሞ ልጀች ላይ እየተገበረ ይገኛል::
ከነዚህ የወያኔ የማፍያ ስልቶች መሃከል ጥቂቶቹን ለመጥቀስ ያክል የሰዎችን መውጣትና መግባት በመጠበቅ በመኪና ገጭቶ መግደል እንደዚሁም ሽፍታ የገደለ ለማስመሰል የታጠቁ ሰራዊቶቹን ጫካ ዉስጥ በማስቀመጥ የሚፈልጉትን ሰው በማስገደል እንደዝሁም አንዱን ለማሰር ለላዉን ለመግደል በሚፈልጉበት ጊዜ ደግሞ ስውር ስራቸዉን ለመፈጸም ለአንዱ ጥይት በመስጠት ለላውን አስገድለው ወያኔ ከዜሩ ውጪ ለማንም ዘመድ መሆን ስለማይችል ገዳዩንም ወንጀለኛ ነህ በማለት በአንድ ድንጋይ ሁለት ወፍ የሚለውን አባባል በስዉር ስራቸው ሲተገብሩት እናያለን። የእርሱ የፖለቲካ ተቀናቃኝ ሰዎችን ድርጅት በመፈለግ በካድረዎቹ በተቀናበረ የፈንጂና የቦምብ ፍንዳታዎች ንፁሃን ዘጎች ባሉበት ቦታ እያፈነዳ በአንድ በኩል እርሱን የሚቃወሙ ሰዎችን ንብረት ሲያወድም በለላ በኩል የንፁሃንን ደም ማፍሰሱ ለማንም ግልፅ ነው። እንደማስተባበያ ሲወስድ ግን የኦሮሞን ህዝብ እና የኦነግን ድርጅት አላማ በለሎች ዘንድ ለማጥቆርና ጠላትነትን ለማብዛት እንዲሁም የሚፈልገዉን የኦሮሞ ልጆች ለማሰር ኦነግ ነው ያፈናዳው ብሎ ተሳስቶ እንኴ እውነት ተናግሮ በማያውቀው ሚዲያው(ETV) በኩል ታፔላ ለጥፎ መለፈፉና የዉሸት ፍርድ ሲሰጥ ማየቱ የወኔን አሸባሪኔትና የሽፍተኝነት ባህሪውን ይገልፃል። ያለምንም ወንጀል ታፍነው በመያዝ በተሰቦቻቸው እንኴ የት እንደደረሱ ሳያውቁ ታስረው ለዘመናት የሚሰቃዩትንና በየ እስር ቤቱ በተለያየ አይነት ዘዴ በስውር የሚገደሉትን የኦሮሞ ልጀች ደግሞ እስር ቤቱ ይቁጠራቸው::
የኢኰኖሚ አውታሮችን ጠቅልሎ በመያዝ የኑሮ ዋስትናን ማሳጣት
ከነዚህ ዋና ዋና የግድያ ስልቶች በተጨማሪ ደግሞ በኦሮሞ ህዝብ ላይ ጠላትነት በመፍጠር ህዝቡን ከህዝብ ጋር ማጋጨትና የትግል አቅም ለማሳጣት ህዝቡን መለያየት የኢኮኖሚ እድገትና የእውቀት እድገት እንዳይኖር ማድረግ ሃብትና ስልጣን እዉቀትና እዉቅና በገዢ ፓርቲ ዘሮች ቢቻ እንዲሆን ማድረግ ከዋነኛዎቹ የወያኔ ስራዎች ጥቂቶች ናቸው::
እንደ ምሳሌነትም በሃገር ዉስጥ የሚኖር የትኛውም የኦሮሞ ተወላጅ እና የኦሮሞ ስም ያላቸዉ ሰዎችን ጨምሮ በነ አፄዎቹ ግዘ የኦሮሞ ስም ማዉጣት እንደ ሃጥያት የሚቆጠርና በአከባቢዉ ገዢዎች ተጠርተዉ ወላጆች የልጆቻቸዉን ስም እንዲለውጡ ከመነገር አልፎ የሚያወጣዉ ስም ምን አይነት ስም መሆን እንዳለበት ከማስጠንቀቅያ ጭምር የሚነገረዉ እንደነበረ የቅርብ ግዘ ትዝታ ቢሆንም ዛሬ ደግሞ የወያኔ መንግስት እንደነ አፄዎቹ የወጣዉን ስም እንዲቀይር ባያደርግም እንኳ የኦሮሞን ህዝብ የሚለይበት መለያ አድርጎ ሲጠቀምበትና እንኴን ኦሮሞ ሆኖ የኦሮሞ ስም ያለው ማንኛዉም ግለሰብ በየትኛውም መስራ ቤትና የስራ መስክ ተሰማርቶ እንዳይሰራ የመስራት መብቱን ተነፍጎ በካድረዎቹ እየተሰደበና ሞራል በሚነካ ኪፉ ንግግር ብቃት እያለው ብቃት እንደለለው በመቁጠር የኑሮ ዋስትናን ማሳጣትና ኢኮኖሚውን በስሩ ጠቅልሎ በመያዝ የትኛውም የኦሮሞ ህዝብ ለትግልና ለነጻነት መክፈል የሚገባዉን እንዲከፍል የሚገፋፋውና የምያነሳሳው የወያኔ ክፉ ስራ መሆኑ ሊጠቀስ ይችላል::
የኢኮኖሚው በአንድ ገዢ መንግስት ዘር መጠቅለሉ በሃገር ዉስጥና ከሃገር ውጪ ያሉ ካምፓኒዎች በሙሉ የመላው የትግሬ ህዝብ ባይሆንም በጥቂቶች በስልጣን ላይ በተፈናጠጡ ትግሬዎች የሚንቀሳቀሱ ስለመሆናቸው ግልፅ ነው:: በዝርዝር ማቅረብ ብያስፈልግ ከ500 በላይ ካምፓኒዎች የነሱ እንደሆነ በተለያየ ግዜ በጋዘጣዎች ላይ የወጣዉን መመልክት ይቻላል ። በዱባይና በለሎችም የአረብ ሃገሮች የተለያዩ ትልልቅ ድርጅቶችን ከፍተው እየሰሩና በለላው ህብረተሰብ ላይ ጫና እየፈጠሩ ስለመሆናቸው ደግሞ የአደባባይ እውነት ነው:: የውጪን ንግድንም በሚመለከት ደግሞ የፓርቲው የዘር መንግስት ዝርያ ካልሆነ በስተቀር እቃው ከሚሸጥበት ዋጋ በላይ ቀረጥ በመጫን የገዢው ፓርቲ ዘር ከሆነ ግን ቀረጥ ነፃ እቃዎችን በማስገባት የለሎችን የኑሮ ዋስትና እያሳጣና እያስመረረ እንዲሰደድ እያደረገ ይገኛል::
የእነሱ ሹማምንት በሃብት ላይ ሃብት፤ በድሎት ላይ ድሎት፣ በእውቀት ላይ እውቀትን ሲጨምሩ፣ የአብዛኛው ኦሮሞ ህዝብ እጣ ፈንታ ግን መፈናቀል፣ መሰደድ፣ መንገላታት፣ መታሰር፣ መደብደብና መገደል ነው።የወያኔ ዘሮች የኦሮሞን ሀብትና ንብረት እየዘረፉ ሲጸድቁና የተንደላቀቀ ኑሮ ሲኖሩ ለላውም ህብረተሰብ በተጨማሪ በኦሮሞ መሬት ላይ የትልልቅ ፎቆችና ካምፓኒዎች ባለበት በመሆን ሲበዘብዙና ሲዘርፉ መከላከያ ያጣው የኦሮሞ አርሶ አደርና የኦሮሞ ወጣት ግን በሀገሩና በየ ስደት በረሃው ላይ በረሀብ ጠኔ እየተሰቃየና እየረገፈ ይገኛል።
እንደ ኦሮሞነት ሳስብ ብዙ ግፎችና በደሎች ተፈፅሞብናል እየተፈጸመብን ነው ። ከዚህ በላይ ግን ምን እስከምንሆን እንደምንጠብቅ አላውቅምም ወይም አልገባኝም።
ጭራሽ አሁን ደግሞ ገና የኦሮሞ ስም ሲነሳ ሁሉም በአንድነት እሳት ጎርሰው እሳት ለበሰው ይነሱብን ጀምረዋል ። ይህ ሁሉ የምያመለከተው ከወደ ሰሜን የሚነሳ ሁሉ የጭካኔ፣የገዳይነት፣የዘረፋና የለላውን ማንነት የማንቋሸሽ መንፈስ እንጂ የቅንነትና የርህራሄ መንፈስ የለለው መሆኑን ነው።ከእንግዲህ ግን በበኩሌ እንዲህ አይነት ጭካኔ በሁሉም አቅጣጫ በከበበንና ሊያጠፋን አፉን በከፈተብን ዘመን ውስጥ ሆነን የዋህነታችን ከኛ ጋር መቀጠል የለበትም ባይ ነኝ ።ምክንያቱም እንደዚህ አይነት በክፋትና በጭካኔ ከተሞሉና ትንሽ ይሉኝታ እንኳ ከለላቸው የገዢ መደቦች ጋር ኦሮሞ መኖር የሚችልበት ደረጃ ላይ አይደለም።ይቀጥላል
ድል ለተጨቋኙ የኦሮሞ ህዝብ!
getinetdinkayeh

Monday 16 December 2013

Ethiopian women pay high price for US aid abortion restrictions

Reproductive health has risen up aid donors’ agendas, but USAid rules mean NGOs are shying away from abortion work

By Claire Provost, Addis Ababa
The Kirkos clinic, which performs abortions in Addis Ababa, Ethiopia. Photograph: Marie Stopes International
The Kirkos clinic, which performs abortions in Addis Ababa, Ethiopia. Photograph: Marie Stopes International
Dec 16, 2013 (The Guardian) — Just 1km away from the African Union conference centre, and the international evangelical church in Addis Ababa, the Kirkos health clinic feels far from the politicking and religious opposition that continue to stalk abortion – one of the most contentious global health issues.
Outside, a blue and white sign displays the range of services on offer. Safe abortion tops the list, stenciled in big bold letters, followed by HIV testing, family planning and infertility treatment. Inside, the clinic’s orderly waiting room is already full. It’s 8.30am. Most visitors are young, between 18 and 25 years old, and nurses talk candidly about sex.
While abortion remains a radioactive issue in the US, a number of developing countries have liberalised their abortion laws in recent years, often citing alarming public health statistics. Globally, the World Health Organisation estimates that 47,000 women die from unsafe, “back-alley” abortions each year, and millions more are left temporarily or permanently disabled.
In 2005, Ethiopia legalised abortion in cases of rape or incest, for all young women under the age of 18, and in a number of other situations. Guidelines from the ministry of health in 2006 went further, expanding the range of health facilities allowed to provide abortion services and instructing health workers that women seeking abortions do not have to provide proof of rape or incest, or of how old they are.
The Kirkos clinic, run by the NGO Marie Stopes International (MSI), saw up to 13,000 patients last year, more than 8,500 of whom seek abortions. Being able to offer and advertise a range of services is critically important, says Shewaye Alemu, area manager for MSI in Addis, the Ethiopian capital. It means women can walk into the clinic without disclosing to the world whether they are seeking an abortion, she says.
But despite having one of the most liberal abortion laws in Africa, progress on expanding access to services has been slow, particularly in rural areas. If the Kirkos clinic shows what is possible under Ethiopia’s new law, it is still the exception rather than the norm.
Some 200km from Addis, in the West Arsi zone of Ethiopia’s Oromia region, the Buta health post stands in a small valley.

Inside, the walls of the small, two-room building are covered with hand-drawn tables charting community progress on vaccinations, malaria treatment, use of contraception, and other targets. Staffed by a small team of community health workers, the Buta post serves more than 4,000 people in nearby villages and is one of thousands of such facilities built by the government to extend services into rural areas.
But while women visiting the health post can get their children vaccinated, have contraceptive implants fitted and deliver babies a woman seeking an abortion would have to travel dozens of kilometres to find someone to carry out the procedure.
Staff at the health centre, 8km away, the next rung up in Ethiopia’s multi-tiered healthcare system, say the person trained to provide abortions left a year ago and has not yet been replaced. Women who arrive looking for abortion information and services are referred to the public hospital or NGO clinic in the towns of Awassa (19km away) or Shashamane (26km).
Figures from 2008, the most recent statistics, suggest just 27% of abortions were safe procedures carried out in health facilities. Many women remain unaware of their rights, and where they can access services. Stigma around abortion also persists, particularly for young and unmarried women, and the quality of care available varies dramatically across the country. In 2008, only two-thirds of health facilities were sufficiently equipped to provide basic abortion care, treatment for post-abortion complications, and antibiotics; just 41% of the primary care facilities on which most rural women rely offer basic abortion services.
According to some human rights lawyers and public health NGOs, Ethiopia is a prime example of how controversy about abortion in the US continues to limit women’s access to safe services, even in countries where it is legal. While reproductive health issues and efforts to end maternal deaths have risen up the agenda of aid donors, very few are willing to fund abortion. The largest global health donor, the US Agency for International Development (USAid) attaches anti-abortion restrictions to all of its foreign assistance.
“There is increasing recognition by the international community of the impact of unsafe abortions on maternal mortality. But funding does not reflect this,” said Manuelle Hurwitz, senior advisor on abortion at International Planned Parenthood Federation.

US funding flaws

The Buta health post is part of a massive USAid programme, which aims to reach more than half the country’s population and help reduce maternal and child mortality by supporting integrated family healthcare. The programme does not fund safe abortion – though it does support some services for women suffering health complications following unsafe abortions.
Pathfinder, the US NGO that implements the USAid programme in Ethiopia, says this is a “missed opportunity” and that it is actively looking for other sources of funding so that abortion services can be offered too.
“Any primary health clinic that doesn’t provide abortions is a missed opportunity,” said Demet Güral, a physician and vice-president of programmes at the NGO. Even if women have access to contraception, there are always failure rates, says Güral, and it is essential they can access safe abortion if needed. “Especially for youth; most are not married, they have a future. How can you talk about family planning for youth and not talk about abortion? It’s nonsense.”
While US president Barack Obama repealed the ‘global gag rule’, which prohibited foreign NGOs from receiving US funding if they performed or promoted abortion, anti-abortion restrictions remain attached to US foreign assistance through a relatively obscure and often misunderstood amendment, attached to the US foreign assistance act.
The Helms amendment, first enacted in 1973, says no US aid can go towards abortion “as a method of family planning” or to “motivate or coerce any person to practice abortions”. What this means is open to interpretation, however. In practice, USAid has implemented the Helms amendment as an absolute ban on abortion.
Liz Maguire, CEO of IPAS, a US-based NGO, says Ethiopia is “one of the best examples” of how these restrictions can impact on women’s lives. “Abortion is the most neglected area in women’s health,” said Maguire, who worked for USAid for decades and was head of its population assistance programme during the Clinton administration. “Here, what’s sad is that women are being discriminated against because they live in areas with USAid funding.”
Güral said it is a sad fact that most of the world’s deaths due to unsafe abortions happen in developing countries, where US foreign aid is a critical resource. Many NGOs shy away from working on abortion because they fear the ‘global gag rule’ could return, or are confused about which specific services are allowed under the Helms amendment, she added. “On the ground … we have a ‘let’s not go there’ feeling. That’s the chilling effect,” said Güral. “Of course this is affecting the lives of women.”
• Claire Provost travelled to Ethiopia with Pathfinder
Source: The Guardian

የኦሮሞ ጥያቄዎች ድሮና ዘንድሮ በጨረፍታ

የኦሮሞ ጥያቄዎች ድሮና ዘንድሮ በጨረፍታ
የኦሮሞ ጉዳይ ስነሳ ለምትደነግጡ ሁሉ ገና እልፍ አእላፋት ጊዜ እልፍ አእላፋት የኦሮሞ ጉዳዮች ስለምነሱ አትደንግጡ! ድንጋጤው በዚህ ከቀጠለ ተናችሁ ሁሉ ልታልቁ ነዋ!!! “በቁቤ” አይደለም፤ “በላትን አልፋቤትም” አይደለም የኦሮሞን ጉዳይ በራሳችሁ ፊደል ልናንፀባርቅባችሁ ነው፡፡ ቅንና በጎ አሳቢ ከሆነችሁ ጨረሩ አይጎዳችሁም፡፡ ድብቅ አጀንዳ ካላችሁና የኦሮሞን ጉዳይ የምትፈሩና ኦሮሞን እንደ ስጋት ምንጭ የምታዩ ከሆነ በፊደላችሁ ወደ እናንተ የምናንፀባርቃት የኦሮሞ ጉዳይ ጨረር ሆነ ልታነስራችሁ ትእላለች!!! 

ግን ኦሮሞን ለምንድነው እንደስጋት ምንጭ የምታዩት??? የምሬን ነው እኮ!!! ከጥንት ጀምሮ እስከ አሁን ያው ኦሮሞ መይም ኦሮሚያን የተመለከተ ነገር ስነሰ ሁሉም ፊቱ ይጠቁራል፡፡ እውነት ኦሮሞና ኦሮሚያ ክፉ ሆነው ነው ወይ? አይደለም!!! እናንተም አስረግጣችሁ ታውቃላችሁ…ግን የኦሮሚያና ኦሮሞ ጉዳይ ስነሳ ሰዉ እንዲህ ፊት የምከሰክስበትና በፍርሃት የመናጥበት የሆነ የተደበቀ ምስጥር እንደለ ይሰማኛል፡፡ ማንነት ከሆነ ማንነት ማንነት ነው ለምን የሌላ ብሄርና ብሄረሰብ የማንነት ጉዳይ ስየሳ ሰዉ ብዙም አይጨነቅም? የኦሮሞ ሲሆን ጠባብ፡ ዘረኛ፡ ፀረ-ኢትዮጵያ ወዘተ በዘመቻ መትመም ለምንድነው? የሆነ ከድሮ ጀምሮ አሁንም የምትፈሩ ነገር አለ ማለት ነው፡፡ ይሄ ድሮም ነበረ አሁንም ያለ ትልቁ ችግር ነው፡፡

ቆይ ቆይ…የኦሮሞ ጥያቄ ተመልሷል ብላችሁ ልትሸውዱን የምትሞክሩ ባለተረኞች የኦሮሞ ጥያቄ በቋንቋው የመናገር መብት ብቻ ነው እንዴ? የድሮዎቹ ቋንቋችንና ባህላችንን ጭምር ልነፍጉን ሞከሩ፡፡ ማንነታችንን ለመሰረዝ ሁላ ደነፉብን፡፡ በዚህ መሃል ስንትና ስንት ግፍ ተፈፀብን፡፡ ትልቁን መዘውር ኢኮኖሚውንና ፖሊትካውንም ጠቅልለው ያዙና በገዛ ቤታችን የበይ ተመልካች አደረጉን፡፡ የዛሬዎቹ ባለተረኞቹ መጡና ቆምንለት ያሉት አላማ እንደሽፋን ይዘው ባለተረኞች ሆኑብን፡፡ ቋንቋችሁን፤ ባህላችሁን አንድታሳድጉ ዕድል ተሰቷችኋል አሉን፡፡ ጥሩ አልናቸው!!! ግን ሌላ ብዙ ጥያቄዎች አሉን አልናቸው፡፡ ጀመርን…የእጃዙር ጉዞ አይመቸንም ኣልናቸው፡፡ ኦሮሚያና ኦሮሞ ከኢኮኖሚው በሚገባው መጠን መጠቀም ግዴታ መሆኑን አቋማችን መሆኑን አስረግጠን ነገርናቸው፡፡ ስልታዊ መሰርሰርና በእጃዙር መበዝበዝ እያንገሸገሸን ነው ኣልናቸው፡፡ በፖሊትካም ስልጣን ቢሆን አንዱ አድራጊ ፈጠሪ አንዱ ጉዳይ አሰፈፃሚ ሆኖ መጓዙ እስከመቼ ይቀጥላል ብለን ትልቅ ቅሬታ እንዳለን ነአደባባይ ተናገርን? ለዚያውም ለዚህች ሀገር ህልውና ትልቁን እያበረከትን!!!! ከዚያም “በፀረ” የምጀምሩ ቁጥር ስፍር የሌላቸውን ቃለት ለጠፉብን!!! 

እናማ አንድና አንድ ነገር እንነጋገር….ኦሮሞ ፍትሃዊነት ካለ በኢትዮጵያ ጥላ ስር መቀጠል ችግሩ አይደለም፡፡ በፊት ከነበረውና አሁን ካለው ዓይነት የተሻለ ሁኔታ እንፍጠር ከተባለ በሩ ዝግ አይደለም፡፡ መቼም ዝግ አያደርግምም!!! ግን ሰዉ አጉል ብልጥነት ስሞክርና ኢፍትሃዊነት ስነግስ ዕዳ ኣለብን አንዴ ሁላ ያስብላል!!!///

Saturday 14 December 2013

OLF condemns Ethiopian state terrorism along the Oromia-Kenyan border

                                       
                                            PRESS RELEASE
                                           December 14, 2013

The Ethiopian regime has, once again, orchestrated a widespread unrest and carnage on both sides of the border between Kenya and Oromia. Having totally dominated and dehumanized the Oromo people under its direct control for the past two decades, the regime has exported its terror across the border to the Oromo citizens of Kenya.
We are gravely concerned that the on-going fighting in the Moyale district between Borana, Sakuye and Gerri communities on one side and Gabra and Burji on the other is threatening the very existence of these communities.
So far, the clashes have caused loss of human life and destruction of property. More than 35 people, including women and children, are killed, and hundreds of houses (mostly belonging to Borana) are burnt down. Over 22,000 people are displaced and exposed to an immeasurable suffering.
The Ethiopian regime is the main cause and instigator of this inter-clan conflict. Ethiopian security agents and military forces have been involved in this sort of inter-clan clashes for years and they are intensifying it this time by committing the following sinister acts of divide and rule:

  1. Providing military training and arming rival communities both in Kenya and Ethiopia and incite one against the other and triggering clashes on both sides of the border.
  2. Escorting the rival communities along the border areas when smuggling guns and ammunitions to Kenya.
  3. Allowing some of the rivals groups to organize as militias and granting them safe pass across the border.
  4. Disguising themselves as one of the fighting clan militias they raid the villages of the clans they consider enemies, kill and maim their men, women and children, and loot and burn their homes. They also openly cross over to Kenya in their full military uniform and attack defenseless innocent Kenyan civilians.
  5. Crossing the border and hunting down to abduct or assassinate prominent Oromo-Kenyans and Oromo refugees in Kenya.
  6. The Ethiopian security forces also pay large sums of money bribing the local Kenyan officials who turn a blind eye to the heinous crimes committed on their soil.

The Ethiopian state spreads false propaganda that Oromo Liberation Army (OLA) operates from Kenya as a pretext to cross over and create turmoil in the peaceful adjacent communities in the state of Kenya.

We use this opportunity to refute once again this false and cheap misinformation by the Ethiopian regime that is intended to confuse those who are afar. We appreciate the way the Kenyans live together in peace and equality. We have no motive whatsoever to interfere and disturb the prevailing tranquility of our friendly neighbors.
We urge all concerned to be aware of Ethiopian repressive regime’s malicious scheme of expanding chaos across Ethiopia’s borders to the whole region. The ultimate solution lies with the removal of the terrorist Ethiopian state by the popular struggle which the OLF is leading with determination.
We strongly believe that the communities fighting each other are one people and have no fundamental enmity among them. No matter what happens for the time being, they lived and will continue to live together forever.
We regret that the enemy has succeeded in setting brothers against brothers. However, we are confident the communities will soon overcome the tragedy and resolve the disputes according our African tradition.

In the mean while, at this juncture, we plead to the parties involved in the conflict to resolve differences among themselves harmoniously as they have done for many years in the past. We call upon the Borana, Sakuye, Gerri, Gabra and Burji communities to halt hostilities as a matter of urgency and allow the displaced people to return to their homes.
Let justice prevail all over!
Oromia shall be free!
Source: oromoliberationfront.info
go to link http://ayyaantuu.com/horn-of-africa-news/olf-condemns-ethiopian-state-terrorism-along-oromia-kenyan-border/

Friday 13 December 2013

ጄነራል ሳሞራ የኑስ በውጭ ተቃዋሚዎች የመለስን የበላይነት መስክረዋል አሉ

(ዘ-ሐበሻ) ኢሕአዴግ ለይስሙላ ያከብረዋል እየተባለ በሚተቸውና ለ8ኛ ጊዜ የተከበረውን የኢትዮጵያ ብሄሮች ብሄረሰቦችና ህዝቦች የሕገ መንግሥት ቀን በዓል ምክንያት በማድረግ መንግስት ባሳተመው ‘ሕብረ ብሔር’ መጽሔት ላይ ቃለ ምልልስ የሰጡት የጦር ኃይሎች ኤታማዦር ሹም ጀነራል ሳሞራ የኑስ መለስ ከሞተ በኋላ በውጭ ያሉ ተቃዋሚዎች የሟቹን አቶ መለስ ዜናዊን የበላይነት መስክረዋልና እናመሰግናቸዋለን አሉ። በሰራዊቱ ውስጥ እኩልነት እንዳለ መናገራቸውም ብዙዎችን አስገርሟል።

በከፍተኛ ህመም እየተሰቃዩ ነው በሚል በተደጋጋሚ ተጽፎላቸው የነበሩትና አሁንም ህክምና ሁልጊዜ እንደሚከታተሉ የሚነገርላቸው ጄነራል ሳሞራ ከመንግስታዊው መጽሔት “የቀድሞው የኢ.ፌ.ዴ.ሪ ጠቅላይ ሚኒስትር አቶ መለስ ዜናዊ ህልፈተ ሕይወታቸው በድንገት ከተሰማ በኋላ በውጭ የሚገኙ አንዳንድ ፀረሰላም ኃይሎች እና አንዳንድ ተቃዋሚዎች ኢትዮጵያ ለሽብርና ለሌሎች ፀረ-ሰላም ተግባር መጋለጧ አይቀርም ሠራዊቷም መዳከሙ አይቀርም በማለት ሲገልጹ ነበር። ይህ ሊሆን ያልቻለው ለምንድ ንነው ይላሉ? እነዚህ ወገኖች ይህን ተመኝተዋል ነገር ግን ያልሞከሩት ከምን አንፃር ነው?” በሚል ለቀረበላቸው ጥያቄ በሰጡት ምላሽ “ከመለስ በኋላ ሠራዊቱ ይዳከማል ብለው ማሰባቸው የመለስ አስተዋፅኦ ጠንካራ ሠራዊት እንዲኖር፣ ጠንካራ የኢ.ፌ.ዴ.ሪ መከላከያ ኃይል እንዲኖር ያስቻለ ስለመሆኑ እውቅና መስጠት ስለሆነ እናመሰግናለን።” ካሉ በኋላ ቀጥለውም “ምክንያቱም መለስ ይህቺ አገር ጠንካራ የመከላከያ ኃይል እንዲኖራት ወሳኝ ድርሻ ነበረው ብለው ስላመኑ ነው ይህንን ማንሳት የጀመሩት፡፡ ይህን ማሰብ በመጀመራቸው ደግሞ መመስገን ይኖርባቸዋል፡፡” ብለዋል።ሳሞራ በመንግስታዊው ጋዜጠኛ ለቀረበላቸው ለዚሁ ተመሳሳይ ጥያቄ በሌላ በኩል የአንድ ሰራዊት ጥንካሬ የሚለካው በሰራው አንድ ሥራ ብቻ አይደለም። ሠራዊቱ ይህቺ አገር እስካለች ድረስ አብሮ ይኖራል። ምክንያቱም ተቋሙ ቀጣይ ነው። ተቋሙ ለሁለት ነገር ብቁ መሆን አለበት። አንደኛ ለወቅታዊ ግዳጁ፣ ሁለተኛ ደግሞ ለወደፊት ለሚሰጥ ግዳጅ ብቁና ዝግጁ መሆን አለበት። የእያንዳንዱ አመራር ተልዕኮም ይሄ ነው። በተለይ የከፍተኛ አመራሩ ተልዕኮ ይህንን ማረጋገጥ ነው። ይሄን እንዴት እንፈፅመዋለን ለሚለው ደግሞ ሶስት መሰረታዊ ሥራዎችን በመሥራት ነው።ዋናውና ወሳኙ የሰው ኃይሉን ማዕከል ያደረገ ሥራ መሥራት ነው። የሰው ኃይሉን ማብቃት። ቴክኒካዊና ሙያዊ እንዲሁም አካዳሚያዊ ብቃቱን ማሳደግ፣ ሳይንሳዊ ዕውቀቱን ማዳበር፡፡ እንግዲህ ሶስት የአቅም ግንባታ ሥራ መሥራት ዋነኛው ሆኖ የሰው ኃይል ማዕከል ያደረገ የአቅም ግንባታ ሥራ መስራት ያስፈልጋል። ሁለተኛው ሥራ በአደረጃጀቱና አሰራሩ ሕዝባዊ ባህሪውን እንደጠበቀ ከተልዕኮውና ከባህሪው የሚስማማ አደረጃጀትና አሰራር ያለው እንዲሆን ማድረግ ነው። አደረጃጀት አቅም ፈጣሪ ነው። አደረጃጀት ለዘለዓለም የሚኖር አይደለም። ከሁኔታው ጋር እየዳበረ አቅም እየፈጠረ የሚሄድ መሆን አለበት። አሰራሩም በተመሳሳይ ከሕዝባዊ ባህሪውና ከተልዕኮው የተጣጣመ አሰራር ዴሞክራሲ ያዊና ደስተኛ ሕይወቱን በአስተማማኝ የሚጠብቅ፣ የግዳጅ አስተሳሰቡንና ዴሞክራሲያዊ አስተሳሰቦችን የሚያዳብሩ አሰራሮችን ማረጋገጥ ማለት ነው። አደረጃጀቱም፣ አሰራሩም፣ የሰው ኃይሉም ሦስቱን ሥራዎች በመሥራት ነው ለተጨባጭ ግዳጅም ሆነ ለወደፊት ለሚሰጠው ግዳጅም ዝግጁ የሚሆነው፡፡
“ስለዚህ ሠራዊቱ በዚህ እየተገነባ ስለቆየ ነው ውጤትም እየተገኘ የመጣው፡፡ ካብ አይደለም ሲሠራ የነበረው። ጠንካራ የመከላከያ ተቋም፣ ጠንካራ የመከላከያ ኃይል፣ ሕዝባዊ ባህሪውን የጠበቀ የመከላከያ ኃይል ነው ሲገነባ የነበረው። እና በዚህ ምክንያት ሊፈርስ አልቻለም፡፡ አይፈርስምም ይጠነክራል።
እነዚያ ወገኖች የተመኙትን አልሞከሩትም ማለት ግን አይደለም፡፡ የብተናና የተለያዩ ሥራዎችን አልሞከሩም ማለትም አይደለም። መከላከያ ሠራዊታችንን የሚያፈርሱት ሦስት ምክንያቶች ካጋጠሙ ብቻ ነው የሚል እምነት አለን። በንግግር አይፈርስም። በሦስት ነገር ግን ሊፈርስ ይችላል። አንደኛውና ዋናው ተልዕኮው ከተቀየረ ነው፡፡ እንግዲህ አሁን ተልዕኮው ሕዝባዊ ነው። የወረራ ተልዕኮ የለውም። የሠላም ተልዕኮ ነው ያለው፡፡ ምክንያቱም የኢትዮጵያ ህዝብ ተስፋው ከሰላም እንጂ ከጦርነት አይደለም፡፡ ስለዚህ ከዋናው ተልዕኮ አንደኛው ሠላም ማረጋገጥ ነው። ይህ ደግሞ በሕገ መንግሥቱ የተቀመጠለት ነው። ሁለተኛው ደግሞ የጦርነት አደጋ ካጋጠመ በአጭር ጊዜ እና በአስተማማኝ በመጨረስ ተመልሰን ወደ ልማታችን መግባት ነው።ሌላው ተልዕኮ ደግሞ የአፍሪካ ወንድሞቻችን ከእኛ ለሚፈልጉት ሁሉ አስፈላጊውን ድጋፍ ማበርከት ነው።
የእነርሱ ሰላም የእኛም ሰላም ስለሆነ በአቅማችን በሰላም ማስከበር ሥራ መሳተፍ ነው። አራተኛው ደግሞ በአገር ውስጥ ከፀጥታ ኃይሎች አቅም በላይ የሆነ ጉዳይ ካለ መሳተፍ። በህብረተሰቡ ላይ ሰብአዊና ተፈጥሮአዊ አደጋዎች ከአጋጠሙ የድርሻችንን መወጣት ነው። እነዚህ ተልዕኮዎች ሕዝባዊ ተልዕኮዎች ናቸው። ከሕገ መንግሥቱ የወጡ፣ የተቀዱ ተልዕኮዎች ናቸው።
“ሁለተኛው የሠራዊቱን ጥንካሬ ሊበረብር የሚችል ደግሞ የራሱ የሰራዊቱ የውስጥ ችግር ነው። ኢ-ዴሞክራሲያዊነት ከሰፈነ ሠራዊቱን ሊያፈርሰው ይችላል። ኢ-ዴሞክራሲያዊነት ከተፈጠረ በርካታ መዘዞች ይመጣሉ። ፀረ-ዴሞክራቲክ መሆን ከተጀመረ የህግ የበላይነት ይጣሳል ማለት ነው፡፡ በአንድ በኩል በህግና በአሰራር መሄድ ይቀራል። ሁለተኛ የሠራዊቱ ደስተኛና ዴሞክራሲያዊ ሕይወት ይበላሻል። ስለሆነም ጠንካራ አንድነት፣ አስተማማኝ አንድነት፣ የማይናወጥ አንድነት ያለውን ሠራዊት አንድነቱ እንዲናጋ ያደርገዋል። የጌታና የአሽከር አካሄድ ነው የሚኖረው፡፡ ይሄ ደግሞ ለአገሪቱም ለሁሉም አይጠቅምም።
“ሌላው ደግሞ ሙስና ነው። ሙስና ሠራዊቱን ሊያበላሸው ይችላል፡፡ ሙስና ፀረ ልማት ነው። ሠራዊቱን ሊበትነው እና ሕዝባዊ ባህሪውን እንዲያጠፋ ሊያደርገው ይችላል። አንድ ሠራዊት ሠራዊት ነው የሚባለው እንደ ወታደር እንደ አንድ አካል ሲያስብ እንጂ ለግሉ ሲያስብ አይደለም።
ለምሳሌ አንድ ወታደር በአንድ ሻለቃ ወይም በአንድ ቡድን ሊድን ከሆነ ሻለቃዋ መዳን አለባት፡፡ በሌላ በኩል አስሩ ከዳኑ ነው እርሱ መዳን የሚችለው። ቡድኑ ብቻውን ሊድን አይችልም። ስለዚህ ይሄ ሻለቃ አስሩን ማዳን አለበት።ወታደሩ መዳኑ የሚረጋገጠው አስሩ ከዳኑ ይሆናል። ብቻውን ሊድን ከፈለገ አይችልም። በተመሳሳይ አንድ የመቶ ካለችም ሶስት ቲም አሏት፡፡ የመቶዋ ልትድን ከሆነ ቲሟ መስዋዕትነት መክፈል አለባት፡፡ እንደዛ እያለ ነው የሚሄደው፡፡ ስለዚህ እንደ አንድ አካል የሚያስብ መሆን አለበት፡፡ ፀረ ዲሞክራሲ አካሄድ ካለ በውስጡ አንድነቱ ይላላል፤አስተሳሰቡም ይሸረሸራል ማለት ነው፡፡ ሙስናም በተመሳሳይ ለግል ማሰብን ይመጣል፤ ይህም ያፈርሰዋል። በአጠቃላይ በዚህ ነው የሚፈርሰው እንጂ በንግግርና በአሉባልታ አይደለም።” ብለዋል።
የአንድ ብሔር ተወላጆች በሰራዊቱ ውስጥ ቁልፍ ቦታ መያዛቸው፣ በትውልድ ብሔራቸው የተነሳም በሙስና ነቅዘው ሃብታም መሆናቸውን፣ መከላከያ ሰራዊቱም የሃገር ዘራፊዎች መሳሪያ መሆኑን በስፋት በሕዝብ ዘንድ የታወቀ ሆኖ ሳለ ኤታማዦር ሹሙ ይህንን ሽምጥጥ አድርገው በመካድ ለዚሁ መጽሄት “ወታደር ሲሆን ሕገመንግሥታዊ ሥርዓቱን የመጠበቅ ተልዕኮ ነው ያለው። ሌላ ምንም ነገር የለውም። ከሌላው ዓለም የእኛ ደግሞ ትንሽ ይለያል። ሕገመንግሥታዊ ሥርዓቱ የሚጠበቀው በሕዝቡ፣ በሠራዊቱም በሁሉም እኩል ነው፡፡ የሁሉንም ሕዝቦች ተጠቃሚነት ስለሚያረጋግጥ በተወሰኑ ምሁራን ብቻ የሚጠበቅ አይደለም፡፡ስለዚህ የሁሉንም ህዝቦች ተጠቃሚነት የሚያረጋግጠውን ህገመንግስት ሁሉም ህዝብ ማወቅ አለበት፡፡ ሁሉም ህዝብ ማወቅ አለበት ብቻ ሳይሆን እንዲያምንበትም መደረግ መቻል አለበት፡፡ካመነበት በኋላ ደግሞ እንደወታደር ለመጠበቅም ለመስዋዕት ራሱን ዝግጁ እንዲያደርግ ይገነባበታል።” ማለታቸው ትዝብት ውስጥ እንደጣላቸው ታዛቢዎች ይናገራሉ።

Wednesday 11 December 2013

ወቅቱ የኦሮሞ ህዝብ በይበልጥ ታጥቆ ራሱን የሚከላከልበት እንጂ ባህላዊ ትጥቁ ሳይቀር በጠላት የሚፈታበት ወቅት ሊሆን ኣይገባም


የወያኔ መንግስት የኦሮሞን ህዝብ ዋነኛ የጥቃት ኢላማው በማድረግ ካለፉት ስርኣቶች ሁሉ የከፋ ስለመሆኑ ኣያጠያይቅም። በተቻለለት መንገድ ሁሉ ይህን ህዝብ በማዋረድና በማዳከም ላይ ሲተጋ ይታያል። ወያኔ ለሁለት ኣበይት ጥቅሞች ሲል ከኦሮሞ ህዝብ ጫንቃ ላይ ኣለመውረድን ኣሻፈረኝ ብሏል። የመጀመሪያው የኢኮኖሚ ጥቅም ነው። የኦሮምያን ሃብት ዘርፎ ጡንቻውን እያፈረጠመበት የኣገዛዝ እድሜውን ያራዝምበታል። የወደፊት ኣገሩንም ይገነባበታል። ሁለተኛው የፖለቲካ ጥቅም ነው። ኣለምን በሚያታልልበት የውሸት ዴሞክራሲያዊው ስርኣት ውስጥ የዚህን ብዙሃን ህዝብ ድምጽ በሃይል እየነጠቀ በኣገሪቷ መሰረተ-ሰፊ ድጋፍ ያለው መንግስት ራሱን ኣስመስሎ ኣውጇል። በይስሙላ ፓርላማው ውስጥ በኢህኣዴግ ኣባልነት ብዙሃኑን ወንበር ይዞ ሁሌም ስርኣቱን ከሽንፈት ኣደጋ ሲታደግ የምናየው የኦሮሞን ህዝብ ድምጽ ያላንዳች ጠንካራ የኦሮሞ ተቃዋሚ ፓርቲ ተሳትፎ ራሱ ጠቅልሎት የያዘው ኦፒዲኦ ነው።
የወያኔ መንግስት እነዚህን ሁለት ኣበይት ጥቅሞቹን ለማስጠበቅ ሲል ኦሮሞን ኣስፈራርቶ በኣገዛዙ ስር ለማስቀጠል ደፋ ቀና ይላል። ከህዝቡ መሃል የታጠቁ ወገኖችን ትጥቅ ማስፈታት፣ ከጎሮቤቶቹ ህዝቦች ጋር ማጋጨት፣ ኦነግን ትደግፋለህ እያለው መዝረፍና ማሰር፣ ከዚህም ኣልፎ መግደል ላለፉት 22 ኣመታት ዋነኞቹ የስርኣቱ ተግባሮች ነበሩ። በማንኛውም መልኩ የኦሮሞ ህዝብ ክንድ ጠንክሮ ስጋት ላይ እንዳይጥለው ከመግታት ቦዝኖ ኣያውቅም። በቅርቡ ከምስራቅ ኦሮምያ የሚወጡ መረጃዎች የሚጠቁሙትም ይህንኑ ኣውነታ የሚመሰክር ነው። በነዚህ መረጃዎች መሰረት የወያኔ መንግስት ምእራብ ሃረርጌ ውስጥ የኦሮሞ ተወላጆችን ትጥቅ በማስፈታት ዘመቻ ተጠምዷል። የሚገርመው ደግሞ ከህዝቡ ላይ የሚፈቱት ዘመናዊ የጦር መሳሪያዎች ሳይሆኑ ባህላዊ የልማትና የጦር መሳሪያዎች መሆኑ ነው። ኦሮሞ ዘመናዊ የጦር መሳሪያ መታጠቅ ይቅርና ባህላዊ መሳሪያውን ሳይቀር እንዲፈታ እየተገደደ ነው። በተለይም ጉባ ቆሪቻ እና ገመቺስ ወረዳዎች ውስጥ የስርኣቱ ተላላኪዎች መንጫ በመባል የሚታወቀውን ባህላዊ መሳሪያ ከህዝቡ ላይ የመቀማት ዘመቻ ላይ ተሰማርተዋል። በምስራቅ ኦሮምያው ህዝባችን ዘንድ መንጫ ከበርካታ ክፍለ ዘመናት በፊት ጀምሮ የልማትና የመከላከያ መሳሪያ በመሆን የሚታወቅ ነው። ይህ ብቻም ሳይሆን መንጫ የኦሮሞ ህዝብ የባህል ቅርስም ነው። በዚህ የኦሮምያ ክፍል መንጫ የማንነት መገለጫ ባህል ኣካል በመሆን በዘፈንና በጭፈራ ወቅት ጥቅም ላይ ይውላል። በባህል ኣልባሳት ተውቦ መንጫ በመያዝ ሸጎዬ መጨፈር ከጥንት ጀምሮ የኦሮሞ ህዝብ ባህል ኣካል ነው። በተጨማሪም ቀደም ሲል እንደ ተጠቀሰው መንጫ የልማት መሳሪያም እንደመሆኑ መጠን ገጀራ፣ መጥረቢያና ማጭድ ከመሳሰሉት ቁሳቁሶች ጋር ተመሳሳይ ኣገልግሎት ይሰጣል።
ይህን ባህላዊ መሳሪያ ከህዝቡ ላይ ለመቀማቱ ዘመቻ የተሰጠው መሰረተ ቢስ ምክንያት ደግሞ ‘ህዝቡ በመንጫ እየተጨፋጨፈ ነውና መሳሪያውን ከህዝቡ ኣሰባስበን ወደ ብረት ፋብሪካ በመላክ ወደ ምርት መሳሪያነት እንቀይራለን’ የሚል ነው። ይህ ነጭ ውሸት መሆኑን ህዝባችን በውል መገንዘብ ይኖርበታል። ማንኛውም ዜጋ በዚህ ተራ የወያኔ ቅጥፈት መታለል ኣይገባውም። ከጥንት ጀምሮ በዚህ መሳሪያ በኣግባቡ ሲጠቀም የኖረ ህዝብ ዛሬ ላይ ምን ኣግኝቶት በመንጫ ይጨፋጨፋል? በሃይለ ስላሴና በደርግ መንግስታት ዘመን ኣንድም ጊዜ ኣደገኛነቱ ተነግሮ የማያውቀው መንጫ ዛሬ በወያኔው ዘመን ለምን ለውግዘት በቃ? ይህ ስርኣት ከማናቸውም የኢትዮጵያ ክልሎች በተለየ ሁኔታ ኦሮምያ ላይ በማነጣጠር በተለይም የኦሮሞ ህዝብ መሬት ተቆርሶ ሆን ተብሎ ወደ ሶማሊ ክልል እየተካለለ ባለበት ምስራቅ ኦሮምያ ላይ ይህን መሰል ባህላዊ መሳሪያ የማስፈታት ዘመቻ ለምን ኣስፈለገው? ህዝቡ እነዚህንና የመሳሰሉትን ኣበይት ጥያቄዎችን ማንሳት ኣለበት። የጥያቄዎቹ መልስም እንደሚከተለው ነው።
የዚህ ስርኣት ትልቁ ኣላማ የኦሮሞን ህዝብ ባህላዊ ትጥቁ ሳይቀር ኣስፈትቶት ባዶ እጁን በማስቀረት እንደፈለገው ረግጦ መግዛት ነው። ወያኔ ምስራቅ ኦሮምያ ውስጥ ሁለት ተያያዥ ጸረ ኦሮሞ ዘመቻዎችን ኣንድ ላይ እያከናወነ ይገኛል። ባንድ ወገን የኦሮሞን ህዝብ ኣንጡራ መሬት ቆርሶ ወደ ሶማሊ ክልል በማካለል በሁለቱ ወንድማማች ህዝቦች መካከል ኣደገኛ ግጭት እንዲፈጠር ኣያሰሬ ነው። ‘ልዩ ሃይል’ በተሰኘው ሰራዊቱ ኣማካኝነት ኦሮሞውን ከቀዬው ሲያፈናቅል በተቃራኒው ደግሞ ሶማሊዎችን እስከ ኣፍንጫቸው እያስታጠቀ በኦሮሞ ቀዬ ላይ ያሰፍራል። ከዚሁ ጎን ለጎን በሁለተኛ ተግባርነት የተያያዘው ኦሮሞን ትጥቅ የማስፈታት ዘመቻ ነው። ኦሮሞ ባህላዊ ትጥቁን ሳይቀር ፈትቶ ባዶ እጁን ቀርቶ በቀላሉ እንዲመታ ለማመቻቸት የተያዘ ዘመቻ መሆኑ ነው። ኦሮሞው ቀዬው ላይ ጠመንጃ ቀርቶ ባህላዊ የመከላከያ መሳሪያ እንኩዋን እንዲፈታ በሚገደድበት በዚህ ወቅት ሌላ ሃይል ደግሞ ዘመናዊ ጠመንጃዎችን እስከ ኣፍንጫው ታጥቆ ኦሮምያ መሬት ላይ እንዲሰፍር እገዛ ይደረግለታል። ከዚህ እርምጃ በላይ በኦሮሞ ህዝብ ላይ የተቃጣ ጠላታዊ ጥቃት ታይቶ ኣይታወቅም። በኢትዮጵያ ታሪክ ውስጥ ደርግም ሆነ ከሱ በፊት የነበሩ የፊውዳል ስርኣቶች ኦሮሞ ላይ ብቻ ባነጣጠረ መልኩ ባህላዊ የጦር መሳሪያ ሲያስፈቱ ተሰምቶ ኣያውቅም። ወያኔ ከቀደሙት ስርኣቶች በከፋ መልኩ የኦሮሞ ህዝብ ደመኛ ጠላት መሆኑን ለማረጋገጥ ከዚህ የበለጠ መረጃ ኣያስፈልግም።
ኣሁን በምስራቅ ኦሮምያ የተያዘው ዘመቻ ወደተቀሩት የኦሮምያ ክፍሎችም እንደሚዛመት ከስርኣቱ እኩይ ልምድ መረዳት ይቻላል። የወያኔ ኣላማ ኦሮሞን እንደ ኦሮሞነቱ ባዶ እጅ በማስቀረት በቀላል ጥቃት ማንበርከክ ነውና። ስለሆነም ይህ የከፋ መንግስት ያሰናዳለትን ጥቃት መክቶ ለመመለስ ህዝቡ ካለበት ሁሉ ማመጽ ይጠበቅበታል። የምስራቁም ሆነ የማንኛውም የኦሮምያ ክፍል ህዝባችን የወያኔን ትጥቅ የማስፈታት ዘመቻ ከማክሸፍ ኣልፎ በስርኣቱ ላይ የመልሶ ማጥቃት ክንዱን ማንሳት ኣስፈላጊ ሆኗል። የኦሮሞ ህዝብ በማንኛውም የስርኣቱ ማታለያ መደናገር የለበትም። ‘የጦር መሳሪያን ወደ ልማት መሳሪያ ለመቀየር የተያዘ ዘመቻ ነው’ የሚለው የጠላት ማታለያ ከቶ ህዝባችንን ማሳሳት የለበትም። በኣለማችን ላይ ማንኛውም ህዝብ ለልማት ከሚገለገልባቸው መሳሪያዎች በተጨማሪ ባህላዊ ወይም ዘመናዊ የጦር መሳሪያዎችም ይኖሩታል። የሰው ልጅ እንደ ማጭድ፣ ገጀራና ኣካፋ ባሉት መሳሪያዎች የልማት ስራውን እንደሚያከናውነው ሁሉ ጦር፣ ጎራዴና መንጫ በመሳሰሉት መሳሪያዎች ደግሞ ከጠላት ጥቃት ራሱን ይከላከላልባቸዋል። ከኣደገኛ የዱር ኣራዊቶችም ራሱን ይጠብቅባቸዋል። ይህ የሰው ልጅ ራሱን የመከላከል ተፈጥሮኣዊ መብት ነው። ይህንን ሰብኣዊ መብት ለመግፈፍ የሚደረግ ሙከራ ሲያጋጥም ደግሞ በጋራ ክንድ መቀልበስ የግድ ይሆናል። መንጫም ሆነ ሌላ ማንኛውንም ባህላዊ የጦር መሳሪያ ከህዝቡ ለመቀማት መንደር ለመንደር የሚንከላወሱ የጠላት ተላላኪዎች የህዝቡ የተባበረ ክንድ መቅመስ ይገባቸዋል። ህዝባችን ማንኛውንም ኣይነት ትጥቁን ፍታ ሲባል መፍታት፣ ተንበርከክ ሲባል መንበርከክ ካሁን በሁዋላ ኣስነዋሪና መቆም ያለበት ነው።
በጥቅሉ የወያኔ መንግስት የኦሮሞን ህዝብ ፈርቶ ባህላዊ መሳሪያው ሳይቀር ለማስፈታት የተነሳበት ምክንያት ግልጽ ነው። በመላው ኦሮምያ ህዝቡ በተለያዩ መንገዶች በስርኣቱ ላይ ያፋፋመው የኣልገዛም ባይነት ንቅናቄ ከቁጥጥሩ ውጭ ከሚወጣበት ደረጃ መቃረቡ ነው። በትጥቅ ትግል ላይ ከተሰማሩት ቆራጥ የኦሮሞ ልጆች በተጨማሪ እዚያው የስርኣቱ ጉያ ስር ሆነው በወያኔ ኣደገኛ ካድሬዎች ላይ ኣስደማሚ የጥቃት እርምጃ የሚወስዱ ጀግኖች መበራከታቸው ስርኣቱን ክፉኛ ኣስበርግጎታል። በዚህ ሁኔታ ከቀጠለ ኦሮምያ ከኣጭር ጊዜ በሁዋላ ከእጁ ልታመልጥ መሆኑ ለስርኣቱ የገባው ይመስላል። ለዚህ ደግሞ እንደ መፍትሄ መውሰድ የመረጠው እርምጃ ኦሮሞን ማንኛውም ትጥቅ ኣልባ ማድረግ፣ እርስ በራሱና ከጎሮቤቶቹ ጋር ማጋጨት፣ ባጠቃላይ ከውስጥና ከውጭ ህዝቡን ሰላም ነስቶት የትግል ክንዱን ማላሸቅ ሆኗል። ህዝባችን ግን ይህ የጠላት ምኞት እንዳይሳካ በተባበረ ክንድ መፋለም ብቸኛ ምርጫው ሆኗል። ህሊና ያላቸው የኦፒዲኦ ኣባላት ሳይቀሩ ነገ ከማይቀርላቸው የታሪክ ተጠያቂነት ለመዳን ከፈለጉ ኣንዲህ ባለው ወቅት ህዝባቸው ላይ የሚፈጸመውን ግፍ በግልጽ መቃወም ይጠበቅባቸዋል።
ወቅቱ ለኦሮሞ ህዝብ ተጨማሪ ዘመናዊ መሳሪያዎችን በሚገባ በመታጠቅ ራስን የሚከላከሉበት እንጂ ባህላዊ መሳሪያም ሳይቀር የሚፈቱበት ወቅት ሊሆን ኣይገባም። በተለይም ወጣቱ ትውልድ ቄሮው ኣንደ ቄሮነቱ ባለበት ሁሉ ተደራጅቶ ዘመናዊ የጦር መሳሪያዎችን ከጠላት እጅ እየነጠቀ በመታጠቅ እየተዋረደ ያለውን ህዝቡን ከውርደት ማዳን የወቅቱ ጥያቄ ነው።
ድል ለኦሮሞ ህዝብ!
የኦነግ ኢንፎ ዴስክ

በጅዳ ቆንስል በር ውላ የምታድረው እህት ክራሞት…

 

                                                                                                                                                                          December 11, 2013
                                                                                                                    ነቢዩ ሲራክ
Ethiopian woman in Saudi Arabia, Jiddah Ethiopian embassy
ይህችን እህት በጅዳ ቆንስል መስሪያ ቤት በር ተቀምጣ ካየኋት ሳምንት አልፏል። አልፎ አልፎ ላነጋግራት ብሞክርም መልስ አትሰጥም። መጀመሪያ ያየኋት ቀን አካባቢ ከስራ ለተፈናቀሉ እህቶች አነሰም በዛ መጠለያ እያለ ፣ ለምን በር ላይ ትሆናለች? ብየ የጠየቅኳቸው የቆንስሉ ጸጥታ አስከባሪ “አንተየ የዚህች እህት ጉዳይ አስቸጋሪ ነው ። ከመጠለያው ብዙ ቆይታለች ፣ አሁን በር ላይ የሆነችው ሃገር ቤት ለመሄድ ወረቀቷ አልቆ እያለ “ሃገር ቤት አልሄድም!” በማለቷ እነረደሆነ ተነግሮኛል ። “በመጠለያው የነበሩት ሰነዳቸው ባሳር በመከራ አልቆ ሲሸኙ ወደ ሃገር ቤት አልሸኝም ብላ ረብሻ ከማንሳት አልፎ ከተዘጋጀው መኪና ወርዳ ይህን የምታየው ሚኒባስ መስታውት ሰብራዋለች! ከዚያን ቀን ወዲህ አትበላም አትጠጣም ፣ እኛንም የገረመን ይሄ ነው! ምን ታደርጋለህ! ” ነበር ያሉኝ …
ይህ ከተነገረኝም “ወዲህ ሃገር ቤት አልገባም!” ያለችው እህት ለቀናት በቆንስሉ በር አልጠፋችም። ከተቀመጠችበት ወንበር ጀርባ ባለው ግድግዳ “ህጋዊ ሰነድ የሌላችሁ እና የወጣውን የሳውዲ ህግ መስፈርት የማታሟሉ ወደ ሃገር ግቡ !” የሚለው የቆንስል ማስታወቂያ ይታያል ። ከአጠገቧ በፕላስቲክ ኪስ የታጨቀ ጓዟን አስቀምጣ ፣ በሆዷ ቁርአን ታቅፋ አንገቷን ከመድፋት ባለፈ በአካባቢው አዛን ስትሰማ የዘወትር ጸሎቷን (ሰላቷን) ወንበሯን ፈቀቅ አድርጋ እንደምትሰግድ አንድ ዘወትር እንቅስቃሴዋን የሚከታተል ወዳጀ አጫውቶኛል… እንዲህ ሆና ኮርመት ብላ ውላ ታድራለች! ቀን ጸሃይ ሲወቃት ፣ ማታ ወበቁ ይፈራረቅባታል ! ካየኋት ቀን ጀምሮ ወደ መጠለያው እንድትገባ ብዙ ሁነን ብንማጸናትም አልተሳካልንም …
ከሃገሯ በጤና የመጣችው እህት ችግር ውጋቷን እንድንጋራ ስንጠይቃት አትመልስም! ወደ ሃገር ቤት እንድትገባ በጅዳ ቆንስል ልትሸኝ ቢሞከርም አልተሳካም። የ”ሃገር ቤት ግቢ!” ” አልገባም!” አለ መግባባት ፍርሻ ከመምጣቱ በፊት አንዳንዴ ኦሮምኛና ብዙ ጊዜ ግን የተሰባበረ አረብኛ እየቀላቀለች መናገር ይቀናት እንደነበር አንድ “በመጠለያው እያለች አውቃታለሁ!” ያሉ ወንድም አጫውተውኛል። ያን ሰሞን ወደ መጠለያው እንድትገባ ተለምና ብትገባም በመጠለያው ውስጥ ካሉ ግፉአን ጋር ግብ ግብ ፈጥራ መውጣቷን ሰምቻለሁ!
ይዚህች ግፉዕ እህት ሰላም የነሳና አዕሮዋን ያወከ የውስጥ ህመም ሚስጥር አይታወቅም! ትሰማለች ፣ ለመናገር አልፈቀደችም! ባሳለፍናቸው የበር ላይ ውሎዋ ትንፍሽ ብላ ስትናገር ቢያን እኔ እስከ ዛሬ አልሰማኋትም ! ውስጧ እንጅ ውጭ አካሏ የተጎዳ አይመስልም! ከሁሉም የሚገርመው ይህች እህት ጤናዋ ታውኮ እንኳ ሃገር ቤት ከወገኖቿ ጋር መቀናቀል ሞት መስሏታል ! ሌላው አስገራሚ ሂደት የዚህችን መልከ መልካም እጣ ፈንታ የምንመለከትም ህጋዊ ሰነድ የሌለን ብዙዎች የሳውዲን መንግስት የምህረት ቀቢጸ-ተስፋ ሰንቀን ጤናችን ተጠብቆ እያለ” በሰላም ሃገር ቤት ግቡ!” የሚለውን የመንግስትና የወገን ምክር መቀበል አቅቶናል! እንዴት ነው ነገሩ …?
አንድየ ይታረቀን ከማለት ባሻገር ምን ይባላል :) ብቻ እሱ ያቅልለው እንጅ የሚሰማ የሚታየው ይከብዳል ! … ያማል … ያማል!

Tuesday 10 December 2013

አቶ ሙሐመድ ኢብራሒም ማእከላዊ እስር ቤት ዉስጥ በደረሰባቸው ድብደባ ህይወታቸዉ ማለፉ፤ ሆድ-እቃቸዉ ተከፍቶ ኩላሊታቸዉ መሰረቁ ታወቀ

አስክሬን ሲል በጥቅምት 4/2006 በአካባቢዉ ላይ ፈንድቶ ከነበረዉ ቦንብ ጋር በተያያዘ መልኩ ለምርመራ ማእከላዊ እስር ቤት መግባታቸዉ እና በማእከላዊ ቆይታቸዉ ምግብ እንዳይገባላቸዉ ቤተሰብ እንዳይጠይቃቸዉ መከልከሉም ለማወቅ ተችሏል።

ዋሽንግተን ዲሲ ህዳር 30/2006 (ቢቢኤን) ፦ በአዲስ አበባ ዉስጥ በቦሌ ክፍለ ከተማ ነዋሪ የነበሩት አቶ ሙሐመድ ኢብራሒም ቀደም ሲል በጥቅምት 4/2006 በአካባቢዉ ላይ ፈንድቶ ከነበረዉ ቦንብ ጋር በተያያዘ መልኩ ለምርመራ ማእከላዊ እስር ቤት መግባታቸዉ እና በማእከላዊ ቆይታቸዉ ምግብ እንዳይገባላቸዉ ቤተሰብ እንዳይጠይቃቸዉ መከልከሉም ለማወቅ ተችሏል።


እንደ አቶ ሙሐመድ ጓደኛ አገላለጽ ግለሰቡ ለተጠረጠሩበት ወንጅል የሚያበቃቸዉ ጉዳይ ባይኖርም፤ከገቡበት ማእከላዊ እስር ቤት በደረሰባቸዉ ከፍተኛ ድብደባ በህይወት መዉጣት አልቻሉም።

ለሐያ ዘጠኝ ቀናት ማእከላዊ እስር ቤት የታሰሩት አቶ ሙሐመድ ምን ያህል ድብደባ እንደደረሰባቸዉ ባይታወቅም ጭንቅላታቸዉ በጣም መጎዳቱን፣ሰዉታቸዉ እንደበለዘ፣ብዙ ሰንበሮች መታየታቸዉ፣ሆድ እቃቸዉ ተከፍቶ ኩላሊታቸዉ መሰረቁን ለአስራ ሁለትአመታት የሚያዉቋቸዉ ጓደኛቸዉ በሐዘን ይገልጻሉ።የዱር አዉሬ ቦጫጭቆ የገደለው ይመስላል በማለት ሁናቴዉን የሚገልጹት ጓደኛ ከመንግስት አካላትም ይሁን አስክሬኑ ከመጣበት የሚኒሊክ ሆስፒታል ስል አቶ ሙሐመድ አሟሟት የተሰጠ መረጃ አለመኖሩን፤ በደም በተጨማለቀ ከፈን የተከፈነ አስክሬን ብቻ  መመለሱን ገልጸዋል።
ቤተሰቡ ጉዳዩን ለሰብአዊመብት ተሟጋች ለሆኑ ድርጆቶች እንዳያመለክት ከፍተኛ ዛቻ ደርሶበታል፤በቅርበት የሚያዉቋቸዉ እንኳ በሞታቸዉ ከማዘን በስተቀር ስለ አሟሟታቸዉ ከፍርሃት የተነሳ መናገር አይችሉም በማለት የሚያስረዱት ጓደኛቸዉ ሁሉም ለሞቱ ከደነገጠዉ በላይ አስክሬኑን በማየት ተሸማቋል ይላሉ።
በጥሩ ስነምግባራቸዉ የሚታወቁት አቶ ሙሐመድ ኢብራሒም ሐማኖትን ተግባሪ፣ የቤተሰብ አስተዳዳሪ ከመሆን በስተቀር አገርን ወገንን ሊጎዳ በሚችል የአሸባሪ ተግባር የሚጠረጠሩ አይደልም በማለት በሐዘን የሚናገሩት ጓደኛ ሟቹ የሰባት ልጆች አባት እንደነበሩ ቤተሰቡም ለአደጋ መጋለጹንም አስረድተዋል።
በጥቅምት 4/2006 መንግስት በቂ መረጃ ለህዝብ ማቅረብ ባልቻለበት፤ የመንግስት ደህነነቶች አለም አቀፋዊ ትኩረትን ለመሳብና ፖለቲካዊ ጥቅምን ለመጎናጸፍ በቦሌ ክፍሌ ከተማ አደርሰዉታል ተብሎ በሚነገረዉ የቦንብ ፍንዳታ፤ ማመካኛን ለማግኘት የሱማሌ ብሔር ተወላጅ የሆኑትን የአቶ ሙሐመድ ህይወትን መንግስት መስዋዕት አድርጓል  በማለት አስተያያት የሚሰጡ ወገኖች አሉ።በትላንትና እለትዉ የብሔር ብሔረሰቦችን ቀን በጅጅጋ ከተማ ድረስ ባሸበረቀ መልኩ አከበርኩ ለሚለዉ መንግስት፤ የአገሩን ዜጋ በብሔር ነጥሎ ማእከላዊ እስር ቤት አስገብቶ መግደሉ ለመንግስቱ አሳፋሪ ከመሆኑም ባሻገር የስርዓቱን መላሸቅ አመላካች ነዉ የሚሉም አሉ።
የአቶ ሙሐመድ ኢብራሒም ታስሮ ለህልፈት መብቃት፤ የሆድ እቃቸዉ ተቀዶ የኩላሊታቸዉ መሰረቅ ከፍተኛ ምርመራ የሚያሻዉ ቢሆንም፤በሟች አስክሬን ላይ የተፈጸመው ወንጀል ስርዓቱ በህይወት ባሉ ብቻ ሳሆን በሙታንም ላይ ግፍ እንደሚፈጽም የሚያረጋግጥ ነዉ፤ በሐሰት አስሮ በመደብደብ፣በመግረፍ፣እስር ቤት ዉስጥ ከማሰቃየት አልፎ፤ ታሳሪዎች እስር ቤት ዉስጥ ሲሞቱ ሆድ እቃ ተከፍቶ የሰዉነት አካል መቸርቸር ተጀምሯልና!.. ኢትዮጵያ ወዴት እያመራች ነዉ? የሚለዉ ጥያቄ የብዙሐኑ ነዉ።

Monday 9 December 2013

Ethiopia accused of stoking Moyale clashes


Ethiopia accused of stoking Moyale clashes. Dec 08 2013 01:15 pm
Ethiopia accused of stoking Moyale clashes. Dec 08 2013 01:15 pm
December 9, 2013, Nairobi, Kenya (Standard) — MPs Ali Rasso (Saku), Roba Duba ( Moyale) and Mohamud Ali, a former Moyale MP, Sunday claimed Ethiopia was using its military and local militias to hunt down Oromo Liberation Front (OLF) rebels.
Rasso, a former Kenya army colonel, alleged that about 400 militiamen fighting the OLF in Kenya were behind the anarchy in Moyale.
The leaders blamed the attackers for the burning of more than 100 houses in Butiye and Moyale town. Rasso said a gang in full military uniform went on a torching-spree of houses that belonged to senior Borana personalities.
Among the houses burnt on Saturday morning included that of Butiye Ward Representaive Golicha Galgalo and former MPs, Guyo Halake Liban and Mohammed Galgalo.
‘‘ Moyale was deserted on Friday afternoon and the whole of Saturday. Even the fighters retreated. But some people in military uniform were all over burning houses and killing all those in sight,’’ said Rasso.
The MP claimed the Kenya Defence Forces,  deployed to stop the inter-clan clashes, was collaborating with the Ethiopian military and the militias.
He claimed a detachment of Kenya Army based at Odha has an Ethiopian military liaison officer by the name Kiross. “The Ethiopian government has always had a liaison officer at Odha. This man Kiross is their liaison officer and he is the one,” Rasso claimed.
“‘The Kenyan government in collaboration with the Ethiopian government kicked out the OLF in Moyale in 2010, but the Ethiopians were told by the county government officials that the rebels are still there,’’ said the MP.
Marsabit County Commissioner, Isaiah Nakoru refuted claims that KDF was working with their counterparts from Ethiopia but added that his office had received complaints that fighters in military uniform were sighted in Moyale on Friday and Saturday.
“We are investigating about armed people in military gear who were seen in battle in Moyale. But the report we have so far is that militias were behind the burning of the houses,” said Mr Nakoru.
The administrator added that both the protagonists—the Gabra and Burji on one side and the Borana on the other, are backed by their kinsmen from Ethiopia.
Both Kenya and Ethipoia, he added have deployed soldiers along their common border to ensure that no militiamen cross into Kenya. But both countries have also ensured that those seeking refuge are given a safe haven.
That, however, is restricted to the main crossing border point at Moyale. According to sources outside the Government, 17 people were killed between Friday and Saturday, bringing the death toll to 27 in the past one week.
An estimated 70,000 Moyale Central residents have sought refuge in Ethiopia as Kenya Army moved into the volatile border town with armoured vehicles and helicopter gunships.
Source: Standar Digital News

Sunday 8 December 2013

OLF sends condolence letter on Mandela death


olf_logoHis Excellency Jacob G Zuma
President
Republic of South Africa
Dear Mr. President:
It is with feelings of great sorrow that we in the Oromo Liberation Front and the Oromo people at large learned the passing of Mr. Nelson Mandela, the first elected President of South Africa and a true freedom -fighting icon. On behalf of the Oromo Liberation Front (OLF) and the Oromo people, I wish to convey my deepest condolences and sympathies to you and the people of South Africa during this time of national mourning. The passing of Former President Mandela is a tremendous loss not only to South Africa and Africa alone but to the whole world.
The world and Africa in particular has lost an extraordinary statesman; a true freedom fighter whose moral strength, dedication and determination liberated his people from the evil of apartheid and set a genuine example for the rest of world. This gallant son and leader of Africa, through his unconditional sacrifices and heroism transformed his beloved country, South Africa, into peaceful multiracial nation that continues to serve as an example of a true and genuine national reconciliation in the world.
We, Oromo, have very fond memories of Mr. Mandela’s secret visit to our country in 1962, where he was hosted by General Taddasa Biru, an Oromo hero, founder of the OLF and leader who was murdered by the Ethiopian regime in 1975, while in struggle for the liberation of his own people. General Taddasa Biru trained and prepared Mr. Mandela for armed struggle. Because of this connection in particular, Mr. Nelson Mandela has become a source of inspiration for those of us struggling for freedom, equality, peace and reconciliation. We will greatly miss this freedom icon and giant son of Africa.
History will remember President Nelson Mandela as a great man and hero. Nobel laureate Nelson Mandela’s legacy will live on and inspire generations to come.
At this moment, our prayers are with the people of South Africa and President Mandela’s family in particular and we hope that they will find strength and solace to overcome their sorrow during this period of deep grief.

May his soul rest in eternal peace!
Yours Sincerely,

Dawud Ibsa
Chairman
Oromo Libertion Front– National Council

Saturday 7 December 2013

በወያኔ ስርዓት ውስጥ በሙስና ያልተጨማለቀ ሰው ቢኖር እኔ ነኝ ዓሉ ወ/ሮ አዜብ

የብሄራዊ መረጃና ደህንነት አገልግሎት ሰራተኛ የነበሩት አቶ ወልደስላሴ ወልደሚካኤል ከሁለት ቤተሰቦቻቸው ጋር በተጠረጠሩበት የሙስና ወንጀል ተጨማሪ ክስ ተመሰረተባቸው። “የአቶ ወልደስላሴ እህት የ8ኛ ክፍል ተማሪ ስትሆን ፥ ምንም አይነት የገቢ ምንጭ የሌላት እንደሆነች ነው በክስ መዝገቡ የተገለጸው…ግለሰቧ በ 81 ሺ ዩሮ የተገዛ አንድ ስካቫተር ፣ አውቶሞቢል መኪና፣ በአዲስ አበባ ቦሌና የካ ክፍለ ከተሞች እንዲሁም በለገጣፎ ፣ በመቀሌና አክሱም ከተሞች 3 ሺህ 266 ካሬ ሜትር ቦታዎች በስሟ ተመዝግቧል ፤ በተለያዩ ባንኮችም ከ 8 ሚሊየን ብር በላይ ተቀማጭ ገንዘብም እንዲሁ ተመዝግቧል።…….” ተከሳሾቹ አቶ ወልደስላሴ ወልደሚካኤል፣ የመከላከያ ሚኒስቴር ባልደረባ የነበሩት ወንድማቸው ዘርአይ ወልደሚካኤል፣ እህታቸው ወይዘሪት ትርሃስ ወልደሚካኤልና የቅርብ ጓደኛቸው ዶሪ ከበደ ናቸው ።ተከሳሹ በ 2002 ዓ.ም ቱሪዝም ኢን ኢትዮዽያ ኤንድ ዘ ሆርን ኦፍ አፍሪካ የተሰኘ መጽሃፍ ያሳተሙ ሲሆን ፥ ይህንን መጽሃፋቸውን በስፖንሰር ለማሳተም ባደረጉት እንቅስቃሴም የመንግስት የልማት ድርጅቶች ተቆጣጣሪ ኤጀንሲ ዋና ዳይሬክተር የሆኑትን አቶ በየነ ገብረስላሴ የነበራቸውን ቀና አስተሳሰብ ተጠቅመው ያለአግባብ በልጽገዋል ነው የሚለው የክስ መዝገቡ። መጽሃፉ በመስሪያቤታቸው ስም እንደተዘጋጀ በሚያስመስል ሁኔታ አቶ በየነ የሚመሯቸው የቦሌ፣ የብርሃንና ሰላምና የአርቲስቲክ ማተሚያ ቤት ሃላፊዎች በጋራ የአቶ ወልደስላሴን 3 ሺህ መጻህፍት በ124 ሺህ ብር እንዲያሳትሙ ተደርጓል ነው የሚለው ክሱ።

ማተሚያ ቤቶቹ በርካሽ ያሳተሙት አቶ ወልደስላሴ ከነበራቸው ተሰሚነትና ስልጣን መነሻነት መሆኑንና ይህንን መጽሃፍ ኢትዮ ቴሌኮም ምንም በማይመለከተው 10 ሺህ መጻህፍት የሚታተሙበትን የ385 ሺህ ብር ክፍያ ለአቶ ወልደስላሴ እንዲከፍልም መደረጉንም ነው የክስ መዝገቡ የሚያስረዳው። አቶ ወልደስላሴ የሙገር ሲሚንቶ ኢንተርፕራይዝና የአትክልትና ፍራፍሬ ገበያ ማህበር የቦርድ ሰብሳቢ በነበሩበት ጊዜ ሃላፊነታቸውነ ተጠቅመው ፥ ሁለቱ ድርጅቶች 310 ኮፒዎችን በግድ እንዲገዙ መደረጉም ተመልክቷል። 26 የሚሆኑ ግለሰቦችና ድርጅቶችም እያንዳንዳቸው ከ 25 እስከ 1ሺህ 500 ፥ በጥቅሉ ከ73 ሺህ የሚልቁ ኪፒዎችን ሳይወዱ በግድ እንዲገዙ መደረጉ ፣ ይሄ ሁሉ ሲደረግ ተቋማቱ ለመጻህፍቱ ገንዘብ ከፍለው መጻህፍቱን አለመረከባቸውም ጭምር ነው በክስ መዝገቡ የተዘረዘረው። ተከሳሹ አቶ ወልደስላሴ ባልደረባቸወ የሆኑ አንዲት ሴት ጋር በነበራቸው መቀራረብ የመስሪያቤቱን መኪና በህገ ወጥ መንገድ ነዳጅ እያስሞሉ ግለሰቧ እንደልባቸው በአዲስ አበበባና ከከተማ ውጪ እንዲጠቀሙበት አስደርገዋል የሚለውም ተጠቅሶባቸዋል።
ተከሳሹ ከ2003 እስከ 2004 ዓ.ም አቶ ሳቢር አርጋው የተሰኙ ነጋዴን ለምሰራው ቤት ሴራሚክ ስለጎደለኝ የጣሊያን ስሪት ገዝተህ ስጠኝ በማለት ፥ በስልጣናቸው አስፈራርተዋቸው የ65 ሺህ ብር ሴራሚክ ተቀብለዋል ፣ ከ 2001 እስከ 2005 ባሉት የግብር አመታት አሳትሞ ከሸጣቸው መጻህፍት ካገኘው ገቢ ላይ መክፈል የነበረበትን ከ496 ሺህ ብር በላይ ለመንግስት አስታውቆ አለመክፈሉም ተጠቅሷል። ተከሳሹ ባለ4 ፎቅ የግል ቤቱን ወንድሙ ለሆነው ሁለተኛ ተከሳሽ ዘርአይ ወልደስላሴ ውክልና ሰጥቶና ከመኖሪያ ቤት ውጭ ለሆነ አገልግሎት እንዲውል አድርጎ በ14 ወራት ውስጥ 790 ሺህ ብር ገቢ አግኝቷል ፤ ከገቢው 126 ሺህ ብር የሚሆነው የመንግስት ግብርን ለግብር አስገቢው መስሪያቤት ሃሰተኛ መግለጫ በማቅረብ ሳይከፍል መቅረቱም በክሱ ተመልክቷል። ከዚሁ ቤት ኪራይ መንግስት ከተርን ኦቨር ታክስ ማግኘት የነበረበትን ከ119 ሺህ ብር በላይ ገቢ ሳያገኝ መቅረቱና ተከሳሹ በህገ ወጥ መነገድ ያገኘውን ገንዘብ ማንም እንዳያውቅበት ለማድረግ በሰኔ 28 1998 ዓ.ም ለሁለተኛው ተከሳሽ (ወንድም) ዘርአይ ወልደሚካኤል ሙሉ ውክልና መስጠቱ ተዘርዝሯል።
እንዲሁም ምንም አይነት የገንዘብ ልውውጥ ሳያደርጉ ከ3ኛዋ ተከሳሽ እህቱ ትርሃስ ጋር መጋቢት 24፣ 2005 ዓ.ም የብድር ውል ማድረጋቸውም ተጠቅሷል።በተጨማሪም ተከሳሹ ከእህቱና ወንድሙ ጋር ያለአግባብ አፈሯቸው የተባሉ የገንዘብና የአይነት ሃብቶች በክስ መዝገቡ ተጠቅሰዋል። 1ኛው ተከሳሽ ወልደስላሴ ወደሚካአል ከ1983 እስከ የካቲት 2005 ዓ.ም የብሄራዊ መረጃና ደህንነት አገልግሎት የውስጥ ሰራተኛ ሆኖ ሲሰራ ፥ ወርሀዊ ደመወዙ ከ 1,600 እስከ 6,000 ብር የነበር ሲሆን ፥ ነገር ግን ስልጣኑን እና የነበረውን ተሰሚነት በመጠቀም በፈጸመው የሙስና ወንጀል ከባለ4 ደረጃ ህንጻ ውጪ ፣ ከ3 ሚሊየን ብር በላይ በተለያዩ የግልና የመንግስት ባንኮች ተቀማጭ ማድረጉም ተመልክቷል። 2ኛ ተከሳሽ አቶ ዘርአይ ወልደስላሴ ከመከላከያ ሚኒስቴር በጡረታ እስከሚገለል ድረስ ወርሀዊ ደመወዙ 532 ብር የነበር ሲሆን ፥ በክስ መዝገቡ ተከሳሹ በተለያዩ ባንኮች 5 ሚሊየን ብር የሚጠጋ ገንዘብ ማስቀመጡ ፣ በአዲስ አበባ ቤቴል ቁጥር 3 በተባለ አካባቢ በ74 ካሬ ሜትር ይዞታ ላይ መሰረት የተጀመረበት ቦታ ፣ በአፋር ክልል ከ 1 ነጥብ 4 ሚሊየን ብር በላይ ግምት ያላቸው ሁለት የእርሻ ኢንቨስትመንቶችና 2 ነጥብ 7 ሚሊየን ብር ግምት ያላቸው ሁለት ሎደር ማሽነሪዎችም በስሙ መኖራቸው ተመዝግቧል ።
3ኛዋ ተከሳሽ የአቶ ወልደስላሴ እህት የ8ኛ ክፍል ተማሪ ስትሆን ፥ ምንም አይነት የገቢ ምንጭ የሌላት እንደሆነች ነው በክስ መዝገቡ የተገለጸው።ግለሰቧ በ 81 ሺ ዩሮ የተገዛ አንድ ስካቫተር ፣ አውቶሞቢል መኪና፣ በአዲስ አበባ ቦሌና የካ ክፍለ ከተሞች እንዲሁም በለገጣፎ ፣ በመቀሌና አክሱም ከተሞች 3 ሺህ 266 ካሬ ሜትር ቦታዎች በስሟ ተመዝግቧል ፤ በተለያዩ ባንኮችም ከ 8 ሚሊየን ብር በላይ ተቀማጭ ገንዘብም እንዲሁ ተመዝግቧል።

ከሳዑዲ ወደ ኢትዮጵያ ይጓዝ የነበረው አውሮፕላን በኢትዮጵያዊቷ ነብሰጡር ምጥ የተነሳ ተመልሶ አረፈ



(ዘ-ሐበሻ) ኢትዮጵያዊያኑን ጭኖ ከሳዑዲ አረቢያ መካ የተነሳው አውሮፕላን በውስጡ የከጫነት ኢትዮጵያያን መካከል አንዷ ነብሰጡር ምጥ ላይ በመሆኑ አውሮፕላኑ ተመልሶ የሳዑዲ አረቢያ ጠረፍ ላይ እንዲያርፍ መደረጉን አረብ ኒውስ ዘገበ።

አረብኒውስ በድረገጹ እንዳስነበበው አውሮፕላኑ ከሽሜሲ የስደተኞች መጠለያ የነበሩ ኢትዮጵያውያንን ጭኖ ይጓዝ እንደነበር ገልጾ ነኢማ ከድር እስማኤል የተባለችው ይህችው ኢትዮጵያዊት በምጧ የተነሳ አውሮፕላኑ በጠረፍ ከተማ በጀዛን አውሮፕላን ጣቢያ እንዲያርፍ ከተደረገ በኋላ ወደ ሆስፒታል ተወስዳ ወንድ ልጅ በሰላም መገላገሏን ዘግቧል።
ነኢማ ለዜና ምንጮችትናንት አርብ በሰጠችው ቃል ልጇ በመልካም ጤንነት ላይ እንደሚገኝ ገልጻለች።
የጀዛን ከተማ ሃገረ ገዢ ንጉስ መሃመድ ነስር ለኢትዮጵያዊቷ ጥሩ የህክምና እርዳታ እንድታገኝ አዘው እንደነበር የዘገበው አረብ ኒውስ በሳዑዲ የሚኖሩ ኢትዮጵያውያንም ለወገናቸው ለተደረገው የህክምና እርዳታ ምስጋናቸውን ገልጸዋል ብሏል።

ከሳዑዲ ተመላሽ ዜጎች ንብረታችንን የኢትዮጵያ ጉምሩክ እየወሰደብን ነው ሲሉ አማረሩ

ዛሬ በአዲስ አበባ ታትሞ የወጣው አዲስ አድማስ ጋዜጣ እንዳስነበበው ህገወጥ ናችሁ ተብለው ከሳውዲ አረቢያ ወደ አገራቸው የተመለሱ ኢትዮጵያዊያን፤ ለበርካታ አመታት ለፍተን ያፈራነውን ንብረት ይዛችሁ መግባት አትችሉም ተብሎ ተነጥቀናል፡፡ የፍተሻ ሰራተኞች ሻንጣዎቻቸውን በመፈተሽ፣ ሞባይል ከአንድ በላይ ከያዙ ትርፉን በማስቀረት፣ አዳዲስ አልባሳት እና ኤሌክትሮኒክስ ቁሰቁሶች የተወሰኑትን ብቻ በመፍቀድ እና ያመጡትን ወርቆች ግራም በመቀነስ ንብረታቸውን እየወሰዱባቸው እንደሆነ ተመላሾቹ ገልፀዋል፡፡ መሃመድ አባመጫ የተባለ የሳኡዲ ተመላሽ፤ ከሳውዲ ስድስት ሻንጣ ይዞ መምጣቱን ገልፆ፤ ቦሌ አውሮፕላን ማረፍያ ሲደርስ ግን ከሁለት ሻንጣ በላይ ይዞ መግባት እንደማይችል፣ ከአምስት ሞባይሎችም ሁለቱ ብቻ እነደተፈቀደለት ለአዲስ አድማስ ተናግሯል፡፡ የሳውዲ መንግስት ከአንድ ኪሎ በላይ ወርቅ ይዛችሁ መውጣት አትችሉም የሚል መመሪያ ማሳለፉን የጠቆመው ተመላሹ፤ ንብረቱን እዚያው ጥሎ ለመመለስ መገደዱን ገልጿል፡፡ የሳኡዲ መንግስት እንኳን ከወርቅ በስተቀር ሌላ ንብረታቸውን ሁሉ ይዘው እንዲወጡ መፍቀዱን የገለፀው መሃመድ፤ በአገራቸው ንብረታቸውን እንዳያስገቡ መከልከላቸው እንዳሳዘነው ይናገራል፡፡
ኤሌክትሮኒክስና ለቤተሰቦቹ ያመጣውን ልብሶች ቀረጥ ከፍለህ ነው የምትወስደው በመባሉ፣ ለሁለት ቀን በስደት ተመላሾች በተዘጋጀው ድንኳን ውስጥ ያለምንም ፍራሽና ልብስ ተኝቶ ንብረቱን ቢጠብቅም ማግኘት እንዳልቻለ ገልጿል፡፡ “ሳዑዲም እዚህም ሀገራችን ስንደርስ እየበደሉን ያሉት ሃበሾች ናቸው” ያለው መሃመድ፤ መንግስት በሚዲያ በተሟላና በተደላደለ መንገድ እንደሚቀበለን ቢገልፅም እዚህ የጠበቀን ግን ሌላ ነው ሲል ቅሬታውን ገልፆ “ሌላው ቢቀር እስካሁን ተመላሾቹን የሚያመላልሰው እንኳን የሳዑዲ እንጂ የኢትዮጵያ መንግስት አይደለም” ብሏል፡፡ ከሳኡዲ ካመጣችው ወርቅ ላይ ሃምሳ ግራሙን ብቻ እንደምትወስድ የተነገራት ተኪያ ሙሃመድን ያገኘናት በቁጭት መሬት ላይ እየተንከባለለች ነበር፡፡
ተኪያ እያለቀሰች እንደነገረችን፤ ለ14 ዓመት ሰርታ ከሶስት መቶ ሃምሳ ግራም በላይ ወርቅ እንዳጠራቀመች ገልፃ፤ በተፈጠረው ችግር ምክንያት ከሳውዲ እንድትወጣ ከመገደዷ በፊት ሙሉ ንብረቷን አስቀድማ ብትልክም እስካሁን እንዳልደረሰላት ትናገራለች፡፡ አሁንም፤ ከተመለሰች በኋላ የያዘቻቸውን ሻንጣዎች ለመውሰድ እንዳልቻለች የምትገልፀው ተኪያ፤ በፍተሻ ስም ሰራተኞቹ ሻንጣዋን በርብረው በማየት፣ ያመጣቻቸውን የኤሌክትሮኒክስ እቃዎችና ሶስት ሞባይሎች መውሰዳቸው ሳይንስ፣ ሶስት መቶ ግራም የሚመዝን የወርቅ ንብረቷን እንዳታስገባ መከልከሏን በጩኸት ትናገራለች፡፡ ለምን ንብረቷን እንደከለከሏት ስትጠይቅም “እናንተ ነጋዴዎች ናችሁ፤ በስደተኞች ስም ያለቀረጥ ንብረት ለማስገባት ትፈልጋላችሁ” በማለት ሰራተኞቹ እንደመለሱላት ገልፃ፤ ጉዳዩን ለአለቆቻቸው ለማመልከት ብትፈልግም የሚያናግራት ሰው አለማግኘቷን ጠቁማለች፡፡ በዚሁ ስፍራ ያገኘናቸው በርካታ ተመላሾች፤ የንብረታቸው ጉዳይ እንዳሳሰባቸው ይናገራሉ። ንብረታቸውን ሳይዙ ወደቤተሰቦቻቸው ላለመቀላቀል በሚል የተሰበሰቡበት ካምፕ፣ ምንም ለማረፊያ የተመቻቸ አገልግሎት ባለመኖሩ መቸገራቸውንም ገልፀዋል፡፡ መንግስት የሚሰጣቸውን 900 ብር፣ በትራንስፖርትና በስልክ አገልግሎት እንደሚጨርሱ አክለው ተናግረዋል፡፡
በርካቶች በእቃዎቻቸው መታገድ በመበሳጨታቸው ጭቅጭቅና አላስፈላጊ ውዝግብ ውስጥ ለመግባት መገደዳቸውን ተመላሾቹ ይናገራሉ፡፡ “ስንመጣ የሚሰጠንን ሊሴ ፓሴን አይተው ማስተናገድ ሲገባቸው እነሱ ግን ንብረታችንን እየወሰዱብን ነው” በማለት የሚናገሩት ተመላሽ ዜጎቹ፤ “ምናልባትም ንብረት የላቸውም ብለው አስበውን ይሆናል፤ ነገር ግን በርካታ አመታት ስንቆይ መቼም ባዶ እጃችንን አንመጣም” በማለት በምሬት ይናገራሉ፡፡ “ዛሬ እቃችንን የከለከሉን ነገ ምን ተስፋ ይዘን ነው ተደራጅታችሁ ስራ ስሩ ለሚሉን?” የሚሉት እነዚህ ተመላሾች፤ “በመንግስት ላይ አመኔታ የጣልነው ሳውዲ ድረስ በተወካዮቹ አማካኝነት መጥቶ ባናገረን መሰረት ነበር፤ ነገር ግን የተገባልን ቃል ታጥፏል” ይላሉ፡፡ መንግስት ለጉዳዩ ትኩረት ባለመስጠቱ እና ለቤተሰብ መርዶ ባለመነገሩ፣ ለሚያውቋቸው ቤተሰቦች መርዶ ለመንገር ጭንቀት ላይ መሆናቸው ሌላ ችግራቸው እንደሆነ የተናገሩት ተመላሾች፤ አሁንም ቢሆን ሳውዲ ላይ ሃበሻዎችን በመኪና እየገጩ መግደል የሳውዲ ፖሊሶች የቀን ተቀን ስራ መሆኑን ገልፀዋል፡፡ ታዲያ በዚህ አጣብቂኝ ውስጥ አምልጠው የሚመለሱ ዜጐችን ንብረት መቀማት ምን የሚሉት ተግባር እንደሆነ አልገባንም፤ በማለት አማርረዋል-ተመላሾቹ፡፡ ምናልባትም የፖለቲካ ማራመጃ ሊያደርጉን ነው በማለትም ስጋታቸውን አንፀባርቀዋል፡፡
ተመላሾቹ የተሟላ መጠለያ ተዘጋጅቶላችኋል በተባለበት ቦታ ሳይቀር፣ መተኛ ሥፍራ እንኳን እንዳልተዘጋጀ ሲረዱ ተስፋ መቁረጣቸውን እና ንብረታቸውን እንዳያስገቡ ሲከለከሉ፣ ተመልሰው በህገወጥ መንገድ ለመሰደድ ሙከራ መጀመራቸውን ይገልፃሉ፡፡ በጉዳዩ ላይ መልስ እንዲሰጡን የጠየቅናቸው የውጪ ጉዳይ ሚኒስቴር ቃል አቀባይ አምባሳደር ዲና ሙፍቲ በበኩላቸው፤ “ተመላሾቹ ስለንብረት የሚያነሱትን ጥያቄን በተመለከተ፤ እኛ ተመላሾች በሙሉ ንብረት እንደሌላቸው ነው የምናውቀው“ በማለት ተናግረዋል፡፡ አምባሳደሩ አልፎ አልፎ ባዶ እግራቸውን ከሳዑዲ የተመለሱ እንዳሉ ጠቁመው፤ በሳኡዲ መንግስት ጓዛችሁን ይዛችሁ እንዳትወጡ ተከልክላችኋል በመባላቸው፣ መጀመሪያውኑም ንብረት ይዘው ባለመምጣታቸው ነው፤ ብለዋል፡፡ እነዚህ ዜጎች ከመደበኛ የአየር መንገዱ ተጓዦች እኩል እንደማይስተናገዱና ለብቻቸው ተጠብቀው እንደሚስተናገዱ ገልፀው፤ ምናልባት ከነዚህ ዜጎች ጋር ተቀላቅለው የሚመጡ ሌሎች ሰዎች ስለሚኖሩ እሱን ለማጣራት ንብረታቸው ይፈተሻል እንጂ ማንም የእነሱን ንብረት የሚወስድ እንደሌለ የተናገሩት አምባሳደሩ፤ እንኳን በሀገር ውስጥ የገባ ንብረት፣ ሳዑዲ ያለውንም የላባቸውን ውጤት ለማስመጣት እንደሚሰሩ ተናግረዋል፡፡
የሟቾችን ቁጥር እና ለቤተሰቦቻቸው መርዶ አለመንገርን በተመለከተ አምባሳደሩ በሰጡት ምላሽ፣ አሁን ሙሉ በሙሉ ትኩረታችን በህይወት ያሉ፣ ንብረታቸውን ያጡ እና ጉዳት የደረሰባቸው ላይ ነው፤ ብለዋል፡፡ የሟቾቹን ቁጥር በተመለከተ ግን መንግስት ከገለፀው በኋላ፣ የተፈጠሩ ነገሮች መኖራቸውን አምነው፤ ነገር ግን ቁጥሩ ላይ ተመላሾች የሚሉትና አንዳንድ ሚዲያዎች የሚያወሩት ትክክል ሊሆን ቢችልም የተጣራ ነገር እስካላገኘን ድረስ የሞቱበትን ሁኔታ ለማወቅ ያስቸግራል፤ ብለዋል፡፡ የሳውዲ አየር መንገድ እንጂ የኢትዮጵያ አየር መንገድ በመመለሱ ሂደት ምንም አስተዋፅአ ለስደተኞቹ አላደረገም ለተባለው አምባሳደሩ መልስ ሲሰጡ፡- የሳውዲ አውሮፕላን የሚያመላልሰው እራሱ በማባረሩ ምክንያት ነው፤ ወጪውን የሚችለውም እራሱ ነው ብለዋል፡፡

Friday 6 December 2013

ኑዛዜ ማንዴላ

            


ከገለታው ዘለቀ


መቼም ሰው ሥጋ ነኝና ታከተኝ
እረፍት ለጎኔ ናፈቀኝ
ሩጫዬን ግን ጨርሻለሁ
እምነቴንም ጠብቂያለሁ
እነሆ ከፊቴ ……….
ከሰማዩ ከላይ ኣባቴ
የድል ኣክሊል ተዘጋጅቶልኛል
የሰላም የፍትህና የ’ኩልነት
ደግሞ የህግ በላይነት
ዋንጫዎች ይጠብቁኛል
እስትንፋሴ ሳይለይ ግን ኣንድ ነገር ልበል……..
ኣንቺ ኣፍሪካ………
እትብቴ ስወለድ የተቀበረብሽ
ዘመኔን ሁሉ የሰጠሁሽ
እናት ዓለም ኣዳምጪኝማ
ኑዛዜ ቃሌን ጻፊልኝማ
ኣዳምጪኝማ ልንገርሽ
ምክር ተግሳጼን ልስጥሽ
ብዙህ ተፈጥሮሽን
ቀስተ ደመናነትሽን
ውበትሽ ኣርጊው ድሪሽ
ክብርና ልዕልናሽ
ኣትለይው ካንገትሽ ላይ
ዘመን ሲመጣ በዘመን ላይ
ኣንቺ ደቡባዊት ኣፍሪቃዬ
አትብቴ የተቀበረብሽ እመዬ
እንደገና ኣንድ ነገር ላስተንክርሽ
ኣዳምጪኝ እማ ሆይ እባክሽ
ያኔ በለቅሶ ዘርን ስትዘሪ
የነጻነትን፣ የፍትህን ኣባት ስትጣሪ
ጩኸትሽ ከጸባኦት ገብቶ
ቅንፈረጁን ኣምላክ ኣትግቶ
የኢያሪኮን ግንብ ኣፈረሰው
የግዞት ቤቱን ደረመሰው
የብረት በሩን ኣባተው
እግረ ሙቁንም ኣቀለጠው
ት ዝ ይለኛል……
ስወጣ እስራቴ ተፈቶልኝ
ምናቤ ተከፍቶ እንዲህ ኣሳየኝ
አነሆ ጸሃይ ህጉዋን ሰብራ
የተፈጥሮ ልማዱዋን ሽራ
በደቡብ በኩል ስትወጣ
የዘንባባ ዝንጣፊ ኣምጥታ
ኣየኋትና ደስ ኣለኝ
ተሰፋና ሃሴት ወሰደኝ
ኣይኔ በሮቶልኝ ኣሻግሬ ሳይ
ከጸሃይ መውጪያ ወዲያ ማዶ ላይ
ከኒያ ካሳለፍናቸው ክፉ ዘመናት በላይ
ክምር የመልካም ነዶ ዘመን ተቆልሎ ባይ
የኣሁኑ ዘመን ስቃይ
ሊመጣ ካለው ክብር ጋር ሲተያይ
እንደ ኢምንት ሆኖ ኣየሁትና
የዘንባባ ዝንጣፊ ኣነሳሁኝ
ሰላምና ፍትህን ኣወጅኩኝ
በቀልና ዘረኝነትን ኮነንኩኝ
የኩልነትን እጀታ ኣጥብቄ ኣጥብቄ ያዝኩኝ
ያ ነበር በውነት ያስደሰተኝ
በርጅና ዘመኔ ሁሉ እንደ ንስር የሚያድሰኝ
ኣንቺ ደቡባዊት ኣፍሪካዬ
አትብቴ የተቀበረብሽ እናትዬ
ከምድርሽ ፍሬ በልቼ
ከሖድሽ ጠበል ጠጥቼ
ኣድጊያለሁኝና
ምስጋናዬ ይሄውና
ያ የክረምቱ ጊዜ ኣልፎ
ዶፍ ዝናሙ ደመናው ሁሉ ተገፎ
እሰይ እሰይ ኣጨዳሽን ጀምረሻል
የመኸር ጊዜ መጥቶልሻል
ኣጨዳሽን እጨጂ
በርቺ ሂጂ ተራመጂ
ግን ደሞ ….
ኣንድ ነገር ኣትርሺ
ያን ያፓርታይድ ዘረኝነት እንዲያ አንደጠላሽው
ኣንገፍግፎሽ ኣንዘፍዝፎሽ ወዲያ እንዳልሺው
እንደዚያው እንደጠላሽው ኑሪ
በፍቅር ባቡር ብረሪ
አንዳትመለሽበት ኣደረሽን
ከነፍስሽ ጥይው እባክሽን
በራስሽ ላይ አንደጠላሸው
በሌላውም ላይ አታድርጊው
እነሆ አግዚኣብሄር በሰጠኝ ኣገልግሎት
የፍቅርና የሰላም ክህነት
ውጉዝ ውጉዝ ከመ ኣርዮስ
ውጉዝ ከኣፍሪካ ብያለሁ ዘረኝነትን
ኣምባገነንነትና ኢፍታዊነትን
ኣትብቀሉ በምድሪቱ
ኣትለምልሙ ኣታኩርቱ
ባለም ሁሉ በምድሪቱ
ያለም ህዝቦች ሁላችሁ
የሰው ዘር ሁሉ የሆናችሁ
ከሰላምና ከእኩልነት ገበታ ብሉና ጠጥታችሁ ርኩ
ሰላም በሰላም ላይ ፍቅር በፍቅር ላይ ተኩ
የናቴ ያባቴ ልጅ ኣፍሪካ…………
ኣሁን ስጋዬ ረፍት ብጤ ናፈቀው
መቼም ሰው ነውና ስጋ ነውና ታከተው
ሄዶ ሄዶ ከዚህ ኣይቀርምና
የተፈጥሮ ህግ ኣይሻርምና
እኔ እንግዲህ ሄጃለሁ
ፍቅር ሰላም አኩልነት ላለም ሁሉ አመኛለሁ
ኣበቃሁ ቃሌ ይሄው ነው ኑዛዜየን ኣድርሻለሁ
ሃብቴ ቅርሴ ያለኝ ይሄው
ኑዛዜየ ስጦታዬ እምነቴ ነው..
                                                           ከገለታው ዘለቀ

Thursday 5 December 2013

Nelson Mandela, anti-apartheid icon and father of modern South Africa, dies


December 5, 2013
(CNN) — Nelson Mandela, the revered statesman who emerged from prison after 27 years to lead South Africa out of decades of apartheid, has died, South African President Jacob Zuma announced late Thursday.

Mandela was 95.
“He is now resting. He is now at peace,” Zuma said. “Our nation has lost its greatest son. Our people have lost a father.”
“What made Nelson Mandela great was precisely what made him human,” the president said in his late-night address. “We saw in him what we seek in ourselves.”
Mandela will have a state funeral. Zuma ordered all flags in the nation to be flown at half-staff from Friday through that funeral.
Mandela, a former president, battled health issues in recent months, including a recurring lung infection that led to numerous hospitalizations.
With advancing age and bouts of illness, Mandela retreated to a quiet life at his boyhood home in the nation’s Eastern Cape Province, where he said he was most at peace.
Despite rare public appearances, he held a special place in the consciousness of the nation and the world.
A hero to blacks and whites
In a nation healing from the scars of apartheid, Mandela became a moral compass.
His defiance of white minority rule and incarceration for fighting against segregation focused the world’s attention on apartheid, the legalized racial segregation enforced by the South African government until 1994.
In his lifetime, he was a man of complexities. He went from a militant freedom fighter, to a prisoner, to a unifying figure, to an elder statesman.
Years after his 1999 retirement from the presidency, Mandela was considered the ideal head of state. He became a yardstick for African leaders, who consistently fell short when measured against him.
Warm, lanky and charismatic in his silk, earth-toned dashikis, he was quick to admit to his shortcomings, endearing him further in a culture in which leaders rarely do.
His steely gaze disarmed opponents. So did his flashy smile.
Former South African President F.W. de Klerk, who was awarded the Nobel Peace Prize with Mandela in 1993 for transitioning the nation from a system of racial segregation, described their first meeting.
“I had read, of course, everything I could read about him beforehand. I was well-briefed,” he said last year.
“I was impressed, however, by how tall he was. By the ramrod straightness of his stature, and realized that this is a very special man. He had an aura around him. He’s truly a very dignified and a very admirable person.”
For many South Africans, he was simply Madiba, his traditional clan name. Others affectionately called him Tata, the Xhosa word for father.
A nation on edge
Mandela last appeared in public during the 2010 World Cup hosted by South Africa. His absences from the limelight and frequent hospitalizations left the nation on edge, prompting Zuma to reassure citizens every time he fell sick.
“Mandela is woven into the fabric of the country and the world,” said Ayo Johnson, director of Viewpoint Africa, which sells content about the continent to media outlets.
When he was around, South Africans had faith that their leaders would live up to the nation’s ideals, according to Johnson.
“He was a father figure, elder statesman and global ambassador,” Johnson said. “He was the guarantee, almost like an insurance policy, that South Africa’s young democracy and its leaders will pursue the nation’s best interests.”
There are telling nuggets of Mandela’s character in the many autobiographies about him.
An unmovable stubbornness. A quick, easy smile. An even quicker frown when accosted with a discussion he wanted no part of.
War averted
Despite chronic political violence in the years preceding the vote that put him in office in 1994, South Africa avoided a full-fledged civil war in its transition from apartheid to multiparty democracy. The peace was due in large part to the leadership and vision of Mandela and de Klerk.
“We were expected by the world to self-destruct in the bloodiest civil war along racial grounds,” Mandela said during a 2004 celebration to mark a decade of democracy in South Africa.
“Not only did we avert such racial conflagration, we created amongst ourselves one of the most exemplary and progressive nonracial and nonsexist democratic orders in the contemporary world.”
Mandela represented a new breed of African liberation leaders, breaking from others of his era such as Robert Mugabe by serving one term.
In neighboring Zimbabwe, Mugabe has been president since 1987. A lot of African leaders overstayed their welcomes and remained in office for years, sometimes decades, making Mandela an anomaly.
But he was not always popular in world capitals.
Until 2008, the United States had placed him and other members of the African National Congress on its terror list because of their militant fight against the apartheid regime.
Humble beginnings
Rolihlahla Mandela started his journey in the tiny village of Mvezo, in the hills of the Eastern Cape, where he was born on July 18, 1918. His teacher later named him Nelson as part of a custom to give all schoolchildren Christian names.
His father died when he was 9, and the local tribal chief took him in and educated him.
Mandela attended school in rural Qunu, where he retreated in 2011 before returning to Johannesburg and later Pretoria to be near medical facilities.
He briefly attended University College of Fort Hare but was expelled after taking part in a protest with Oliver Tambo, with whom he later operated the nation’s first black law firm.
In subsequent years, he completed a bachelor’s degree through correspondence courses and studied law at the University of Witwatersrand in Johannesburg, but left without graduating in 1948.
Four years before he left the university, he helped form the youth league of the African National Congress, hoping to transform the organization into a more radical movement. He was dissatisfied with the ANC and its old-guard politics.
And so began Mandela’s civil disobedience and lifelong commitment to breaking the shackles of segregation in South Africa.
Escalating trouble
In 1956, Mandela and dozens of other political activists were charged with high treason for activities against the government. His trial lasted five years, but he was ultimately acquitted.
Meanwhile, the fight for equality got bloodier.
Four years after his treason charges, police shot 69 unarmed black protesters in Sharpeville township as they demonstrated outside a station. The Sharpeville Massacre was condemned worldwide, and it spurred Mandela to take a more militant tone in the fight against apartheid.
The South African government outlawed the ANC after the massacre, and an angry Mandela went underground to form a new military wing of the organization.
“There are many people who feel that it is useless and futile for us to continue talking peace and nonviolence against a government whose reply is only savage attacks on an unarmed and defenseless people,” Mandela said during his time on the run.
During that period, he left South Africa and secretly traveled under a fake name. The press nicknamed him “the Black Pimpernel” because of his police evasion tactics.
Militant resistance
The African National Congress heeded calls for stronger action against the apartheid regime, and Mandela helped launch an armed wing to attack government symbols, including post offices and offices.
The armed struggle was a defense mechanism against government violence, he said.
“My people, Africans, are turning to deliberate acts of violence and of force against the government, in order to persuade the government, in the only language which this government shows by its own behavior that it understands,” Mandela said during a hearing in 1962.
“If there is no dawning of sanity on the part of the government — ultimately, the dispute between the government and my people will finish up by being settled in violence and by force. ”
The campaign of violence against the state resulted in civilian casualties.
Long imprisonment
In 1962, Mandela secretly received military training in Morocco and Ethiopia. When he returned home later that year, he was arrested and charged with illegal exit of the country and incitement to strike.
Mandela represented himself at the trial and was briefly imprisoned before being returned to court. In 1964, after the famous Rivonia trial, he was sentenced to life in prison for sabotage and conspiracy to overthrow the government.
At the trial, instead of testifying, he opted to give a speech that was more than four hours long, and ended with a defiant statement.
“I have fought against white domination, and I have fought against black domination,” he said. “I have cherished the ideal of a democratic and free society in which all persons live together in harmony and with equal opportunities. It is an ideal which I hope to live for and to achieve. But if needs be, it is an ideal for which I am prepared to die.”
His next stop was the Robben Island prison, where he spent 18 of his 27 years in detention. He described his early days there as harsh.
“There was a lot of physical abuse, and many of my colleagues went through that humiliation,” he said.
One of those colleagues was Khehla Shubane, 57, who was imprisoned in Robben Island during Mandela’s last years there. Though they were in different sections of the prison, he said, Mandela was a towering figure.
“He demanded better rights for us all in prison. The right to get more letters, get newspapers, listen to the radio, better food, right to study,” Shubane said. “It may not sound like much to the outside world, but when you are in prison, that’s all you have.”
And Mandela’s khaki prison pants, he said, were always crisp and ironed.
“Most of us chaps were lazy, we would hang our clothes out to dry and wear them with creases. We were in a prison, we didn’t care. But Mandela, every time I saw him, he looked sharp.”
After 18 years, he was transferred to other prisons, where he experienced better conditions until he was freed in 1990.
Months before his release, he obtained a bachelor’s in law in absentia from the University of South Africa.
Calls for release
His freedom followed years of an international outcry led by Winnie Mandela, a social worker whom he married in 1958, three months after divorcing his first wife.
Mandela was banned from reading newspapers, but his wife provided a link to the outside world.
She told him of the growing calls for his release and updated him on the fight against apartheid.
World pressure mounted to free Mandela with the imposition of political, economic and sporting sanctions, and the white minority government became more isolated.
In 1988 at age 70, Mandela was hospitalized with tuberculosis, a disease whose effects plagued him until the day he died. He recovered and was sent to a minimum security prison farm, where he was given his own quarters and could receive additional visitors.
Among them, in an unprecedented meeting, was South Africa’s president, P.W. Botha.
Change was in the air.
When Botha’s successor, de Klerk, took over, he pledged to negotiate an end to apartheid.
Free at last
On February 11, 1990, Mandela walked out of prison to thunderous applause, his clenched right fist raised above his head.
Still as upright and proud, he would say, as the day he walked into prison nearly three decades earlier.
“As I walked out the door toward the gate that would lead to my freedom, I knew if I didn’t leave my bitterness and hatred behind, I’d still be in prison,” he said at the time.
He reassured ANC supporters that his release was not part of a government deal and informed whites that he intended to work toward reconciliation.
Four years after his release, in South Africa’s first multiracial elections, he became the nation’s first black president.
“The day he was inducted as president, we stood on the terraces of the Union Building,” de Klerk remembered years later. “He took my hand and lifted it up. He put his arm around me, and we showed a unity that resounded through South Africa and the world.”
Broken marriage, then love
His union to Winnie Mandela, however, did not have such a happy ending. They officially divorced in 1996 after several years of separation.
For the two, it was a fiery love story, derailed by his ambition to end apartheid. During his time in prison, Mandela wrote his wife long letters, expressing his guilt at putting political activism before family. Before the separation, Winnie Mandela was implicated in violence, including a conviction for being an accessory to assault in the death of a teenage township activist.
Mandela found love again two years after the divorce.
On his 80th birthday, he married Graca Machel, the widow of former Mozambique president, Samora Machel.
Only three of Mandela’s children are still alive. He has 17 grandchildren and 12 great-grandchildren
Symbolic rugby
South Africa’s fight for reconciliation was epitomized at the 1995 rugby World Cup Final in Johannesburg, when it played heavily favored New Zealand.
As the dominant sport of white Afrikaners, rugby was reviled by blacks in South Africa. They often cheered for rivals playing their national team.
Mandela’s deft use of the national team to heal South Africa was captured in director Clint Eastwood’s 2009 feature film “Invictus,” starring Morgan Freeman as Mandela and Matt Damon as Francois Pienaar, the white South African captain of the rugby team.
Before the real-life game, Mandela walked onto the pitch, wearing a green-and-gold South African jersey bearing Pienaar’s number on the back.
“I will never forget the goosebumps that stood on my arms when he walked out onto the pitch before the game started,” said Rory Steyn, his bodyguard for most of his presidency.
“That crowd, which was almost exclusively white … started to chant his name. That one act of putting on a No. 6 jersey did more than any other statement in bringing white South Africans and Afrikaners on side with new South Africa.”
During his presidency, Mandela established the Truth and Reconciliation Commission to investigate human rights abuses during apartheid. He also introduced housing, education and economic development initiatives designed to improve the living standards of the black majority.
A promise honored
In 1999, Mandela did not seek a second term as president, keeping his promise to serve only one term. Thabo Mbeki succeeded him in June of the same year.
After leaving the presidency, he retired from active politics, but remained in the public eye, championing causes such as human rights, world peace and the fight against AIDS.
It was a decision born of tragedy: His only surviving son, Makgatho Mandela, died of AIDS at age 55 in 2005. Another son, Madiba Thembekile, was killed in a car crash in 1969.
Mandela’s 90th birthday party in London’s Hyde Park was dedicated to HIV awareness and prevention, and was titled 46664, his prison number on Robben Island.
A resounding voice
Mandela continued to be a voice for developing nations.
He criticized U.S. President George W. Bush for launching the 2003 war against Iraq, and accused the United States of “wanting to plunge the world into a Holocaust.”
And as he was acclaimed as the force behind ending apartheid, he made it clear he was only one of many who helped transform South Africa into a democracy.
In 2004, a few weeks before he turned 86, he announced his retirement from public life to spend more time with his loved ones.
“Don’t call me, I’ll call you,” he said as he stepped away from his hectic schedule.
‘Like a boy of 15′
But there was a big treat in store for the avid sportsman.
When South Africa was awarded the 2010 football World Cup, Mandela said he felt “like a boy of 15.”
In July that year, he beamed and waved at fans during the final of the tournament in Johannesburg’s Soccer City. It was his last public appearance.
“I would like to be remembered not as anyone unique or special, but as part of a great team in this country that has struggled for many years, for decades and even centuries,” he said. “The greatest glory of living lies not in never falling, but in rising every time you fall.”