Saturday 7 December 2013

ከሳዑዲ ወደ ኢትዮጵያ ይጓዝ የነበረው አውሮፕላን በኢትዮጵያዊቷ ነብሰጡር ምጥ የተነሳ ተመልሶ አረፈ



(ዘ-ሐበሻ) ኢትዮጵያዊያኑን ጭኖ ከሳዑዲ አረቢያ መካ የተነሳው አውሮፕላን በውስጡ የከጫነት ኢትዮጵያያን መካከል አንዷ ነብሰጡር ምጥ ላይ በመሆኑ አውሮፕላኑ ተመልሶ የሳዑዲ አረቢያ ጠረፍ ላይ እንዲያርፍ መደረጉን አረብ ኒውስ ዘገበ።

አረብኒውስ በድረገጹ እንዳስነበበው አውሮፕላኑ ከሽሜሲ የስደተኞች መጠለያ የነበሩ ኢትዮጵያውያንን ጭኖ ይጓዝ እንደነበር ገልጾ ነኢማ ከድር እስማኤል የተባለችው ይህችው ኢትዮጵያዊት በምጧ የተነሳ አውሮፕላኑ በጠረፍ ከተማ በጀዛን አውሮፕላን ጣቢያ እንዲያርፍ ከተደረገ በኋላ ወደ ሆስፒታል ተወስዳ ወንድ ልጅ በሰላም መገላገሏን ዘግቧል።
ነኢማ ለዜና ምንጮችትናንት አርብ በሰጠችው ቃል ልጇ በመልካም ጤንነት ላይ እንደሚገኝ ገልጻለች።
የጀዛን ከተማ ሃገረ ገዢ ንጉስ መሃመድ ነስር ለኢትዮጵያዊቷ ጥሩ የህክምና እርዳታ እንድታገኝ አዘው እንደነበር የዘገበው አረብ ኒውስ በሳዑዲ የሚኖሩ ኢትዮጵያውያንም ለወገናቸው ለተደረገው የህክምና እርዳታ ምስጋናቸውን ገልጸዋል ብሏል።

No comments:

Post a Comment