Saturday 25 January 2014

የእስር ጊዜውን ያጠናቀቀው የኦሮሞ ፌዴራላዊ ዴሞክራሲያዊ ንቅናቄ (ኦፌዴን) ምክትል ሊቀመንበር አቶ በቀለ ገርባ አልተፈታም::

ፍትህ ለበቀለ ገርባ!
የእስር ጊዜውን ያጠናቀቀው አቶ በቀለ ገርባ አልተፈታም::
‹አመክሮ መስጠትም አለመስጠትም መብታችን ነው› የማረሚያ ቤቱን ሃላፊዎች

በእስር ቤት የሚገኘው የኦሮሞ ፌዴራላዊ ዴሞክራሲያዊ ንቅናቄ (ኦፌዴን) ምክትል ሊቀመንበር አቶ በቀለ ገርባ በባለፈው እሁድ የእስራት ቅጣቱን አጠናቆ የነበረ እና መፈታት የነበረበት ቢሆንም እስካሁን ድረስ በእስር ቤት ነው የሚገኘው:: በቅርቡ ከጓደኞቼ ጋር ሆነን ቃሌቲ ሄደን አግኝተነው ነበር፡፡ አመክሮ ለማግኘት እንደ መስፈርት የሚወሰደው፤ በቆይታው ወቅት የነበረው ስነ ምግባር በበቂ ሁኔታ እንዳሟላ እንደተገለፀለት ነግሮናል፡፡

ወደ ማረሚያ ቤት ከመግባቱ በፊት ማእከላዊ ያሳለፋቸው 41 ቀናት ሲደመሩ ነው ባለፈው እሁድ መውጣት የነበረበት፡፡ ማእከላዊ በእስር የቆየባቸው ቀናት መያዝና እና አለመያዝ የማረሚያ ቤቱን አስተዳደር የይሁንታ ፈቃድ ማግኘት እንደሚያስፈልግ ተነግሮታል፡፡ በህጉ መሰረት ከሆነ ግን ማንም መፍቀድ ሳይጠበቅበት ሊደመርለት ይገባ ነበር፡፡ትላንት ይህን ጉዳይ ይዘው የማረሚያ ቤቱን ሃላፊዎች ለጠየቁ ቤተሰቦቹ ‹አመክሮ መስጠትም አለመስጠትም መብታችን ነው› የሚል ምላሽ ተሰጥቷቸዋል፡፡

በቀለን ለመጠየቅ የሚፈልግ በስራ ቀናት ጠዋትና ከሰዓት፤ በእረፍት ቀናት ደግሞ ጠዋት ብቻ ቃሊቲ ማረሚያ ቤት ዞን 2 ሄዶ ማግኘት ይችላል፡፡
Postby MINILIK SALSAWI » 23 Jan 2014, 06:46
ፍትህ ለበቀለ ገርባ!

No comments:

Post a Comment